Amharic Language, Literature and Folklore

Permanent URI for this collection

Browse

Recent Submissions

Now showing 1 - 20 of 435
  • Item
    “የአገልጋይ ገጸባህሪያት አቀራረብ ከ1990 እስከ 2010 ዓ.ም ድረስ በታተሙ የተመረጡ የሴት ደራሲያን ረጅም ልቦለዶች ውስጥ”
    (Addis Ababa University, 2016-01) አበበች ሀብተማርያም; መሀመድ አሊ (ዶ.ር)
    ይህ ጥናት “አገልጋይ ገጸባህሪያት ከ1990 እስከ 2010 ዓ.ም ድረስ በታተሙ የተመረጡ የሴት ደራሲያን ረጅም ልቦለዶች ውስጥ” በሚል ርእስ የተከናወነ ነው፡፡ በተጠቀሱት ሃያ ዓመታት ውስጥ ከታተሙ የሴት ደራሲያን ረጅም ልቦለድ መፃህፍት ውስጥ የጥናቴ ዋና ጉዳይ በሆኑት “አገልጋይ ገጸባህሪያት” ዙሪያ ሽፋን ሰጥተዋል ብዬ ያመንኩባቸውን ሶስት ልቦለድ መጻህፍትን በመምረጥ ጥናቴን አካሂጃለሁ፡፡ ጥናቴን ያከናወንኩባቸው ረዥም ልቦለዶች ሶስት ናቸው፡፡ ፀሐይ መልአኩ በ1996 ዓ.ም ያሳተመችው “ቢስ ራሔል”፣ በ2002 ዓ.ም የታታመው የየዝና ወርቁ “የደራሲዋ ፋይል” እና በ2003 ዓ.ም የታተመው የእንዬ ሺበሺ “የገቦ ፍሬ” ጥናቱ ያተኮረባቸው ልቦለድ መጻህፍት ናቸው፡፡ ይህ ጥናት በተመረጡት ሶስት ረዥም ልቦለድ መጻህፍት ውስጥ የሚገኙ አገልጋይ ገጸባህሪያትን ወደ እዚህ ሙያ የገፋፏቸውን ምክንያቶች ያጠናሁበት ነው፡፡ በተጨማሪም አገልጋይ ገጸባህሪያትን በተመረጡት ልቦለዶች ውስጥ ስንመረምራቸው አይነታቸው ከየትኛው እንደሚመደብና አቀራረባቸው ምን እንደሚመስል መርምሬያለሁ፡፡ የሶስቱ ልቦለዶች ገጸባህሪያት ማለትም የ“ቢስ ራሔል” ራሔል ዳርጌ፣ “የደራሲዋ ፋይል” ፅዮን ታምሩ እና “የገቦ ፍሬ”ዋ ነፃነት ክብሩ ውስብስብነት የሚታይባቸውና በህይወት ውጣ ውረድ መከራቸውን ያዩ ገጸባህሪያት ናቸው፡፡ ቤተሰባዊና ማህበረሰባዊ ጫናዎቻቸውን ለማራገፍ በሚጥሩበት ጊዜ የሚደቀኑባቸውን ሌሎች ፈተናዎች እየተወጡ ወደ ስኬታቸው ለመቅረብ የቻሉ ገጸባህሪያት መሆናቸውን ከታሪኮቻቸው ተገንዝበናል፡፡ ለነዚህ ሶስት ገጸባህሪያት ምንም ነገር በቀላሉ የለም፡፡ ለሚበሉት ቁራሽ እንጀራ እንኳን ሲቸገሩ እንደ ነበር ከየልቦለዶቹ ተረድተናል፡፡ የሚፈልጓትን እያንዳንዷን ነገር ለማግኘት የሚገጥማቸው ልፋትና ጥረት አስጨናቂና አንዳንዴም አሰቃቂ ሆኖ የቀረበበት ሁኔታ አለ፡፡ ይህ ሁኔታ ደግሞ አጠቃላይ ገጸባህሪያቱ ከተሳሉበት ጊዜና ቦታ አንፃር “ለምን ሆነ?” ብለን የምንተቸው አይደለም፡፡ እንደውም የዋና ገጸባህሪያትን ውስብስብ ድርሻ አሳይተውናል፡፡
  • Item
    የጭብጥ ትንተና በየስንብት ቀለማት
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2024-01) መስከረም ኪዳነማሪያም; አየለ ፍቅሬ(ዶ/ር)
    ይህ ጥናት በ2008 ዓ.ም ለህትመት በበቃው የአዳም ረታ “የስንብት ቀለማት” ረጅም ልብወለድ የጭብጥ አቀራረብን ፈትሿል። ልብወለድ ያነሳቸው ርዕሰ ጉዳዮች መሠረታዊነት እንደ ጥናታዊ አነሳሽ ምክንያቶች ተወስዷል። ጥናቱ አይነታዊ ዘዴን ተጠቅሟል። ነገረህላዌን ለመተንተኛነትሲጠቀም፣ መዛግብት ወይም ሠነድ ፍተሻና ጥልቅ ንባብ ደግሞ በመረጃ መሠብሰቢያ ዘዴነት ተጠቅሟል።ሁለት የመረጃ ምንጮችንም ተጠቅሟል።እነሱም ቀዳማይና ካልዓይ ናቸው።ቀዳማይ የመረጃ ምንጩ ትንተና የሚካሄድበት የስንብት ቀለማትረጅም ልብወለድ ሲሆን ካልዓይ የመረጃ ምንጮች የምርምር ዘዴ መፃህፍት ፣የንድፈሀሳብና ተዛማጅ ፅሁፎች ናቸው። የልብወለድን ርዕስ ማጤን፣ የገፀባህርያትን ምልልስ/ የእርስበርስ ግንኙነት መመርመር፣ የመቼት ገለጻና የሀሳብ ድግግሞሽ በመረጃ ትንተናው ወቅት ለጭብጥ ትንተናው አገልግሎት ላይ የዋለ የጭብጥ መፈለጊያ ዘዴዎች ናቸው። የስንብት ቀለማት የጊዜ መቼት ከ1960ዎቹ መጀመሪያ እስከ 1980ዎቹ መጨረሻ ባሉት የጊዜ ሀዲድ ላይ የተዘረጋ ሲሆን በእነዚህ ሁለት አስርት ዓመታት ውስጥ የተከሰቱት አበይት ሀገራዊ ክስተቶች የ1966ቱ አብዮት፣ የወያኔና የሻዕቢያ ትግል እንዲሁም የሌሎች ተቀናቃኝ ፓርቲዎች የስልጣን ሽሚያ እንደ ልብወለድ የታሪክ ማስታወሻ ሆነው ቀርበዋል። የመረጃ ትንተናው ሁለት አበይት ክፍሎች ያሉት ሲሆን የመጀመሪያው ክፍል የልብወለድን አብይ ጭብጥ ሁለተኛው ክፍል ደግሞ ንዑሳን ጭብጦችን ይዞል። ሞት ወይም ስንብት የተፈጥሮ ጠባይና አካል መሆኑን ማርዳት የልብወለድ አብይ ጭብጥ ሲሆን “የ ያ ትውልድ ስህተቶች”፣ የመበዳደል አዘሪትና ጭላንጭል ተስፋዎች ደግሞ እንደ ልብወለድ ንዐሳን ጭብጦች ተዳሰዋል። የ ያ ትውልድ ስህተቶች በ1960ዎቹና 1970ዎቹ የኖሩ ወጣቶች የፈጸሟቸውን ፖለቲካዊ ስህተቶች ተመልክቷል። የመበዳደል አዙሪት ደግሞ በገፀባህርያት መካከል የነበሩ ቁርሾዎችና ጥሎች የተዳሰሰበት ክፍል ነው። ጭላንጭል ተስፋዎች ደግሞ1960ዎች እና1970ዎቹ ውስጥ የኖሩ ወጣቶች ከፈጸሟቸው ስህተቶች እንዲሁም በዘመኑ ከነበረው ሀገራዊ ቀውስ በኋላ የታየውን አንጻራዊ ሠላምና መረጋጋት እንዲሁም አዳዲስ የለውጥ ጅማሮዎች የተበሰሩበት ክፍል ነው።
  • Item
    የቱለማ ኦሮሞ ገዳ ሥርዓት ተፈጥሯዊ እና ሰው ሰራሽ የከበሩ ንዋያት ትዕምርቶች ትንተና
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2024-05) ገናናው ከተማ; ታደሰ በሪሶ (ፕሮፌሰር)
    የዚህ ጥናት ዓብይ ዓላማ የቱለማ ኦሮሞ ገዲ ሥርዓት ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ የከበሩ ንዋያትን ትዕምርቶች ገፅታ መተንተን ነው፡፡ ትዕምርቶቹ በሥርዓተ ከበራና በህዜቡ ህይወት ውስጥ ያሊቸውን ዘርፈ ብዘ ጠቀሜታዎችም ገልጿል፡፡ በተዘዋዋሪ መንገድ ካልሆነ በቀር በዚህ ዓይነቱ ትዕምርታዊ አቀራረብ ከዚህ በፉት የተሰራ ጥናት አላገኘሁም፡፡ ይህም የጥናቱ አነሳሽ ምክንያት በመስኩ ያለውን የዕውቀት ክፍተት ይሞላል የሚል እምነት አለኝ፡፡ ጥናቱ በቀዲማይና ካላዓይ መረጃዎች ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ ከቤተመጻሕፍት የተገኘው ካልዓይ መረጃ ለጥናቱ መመልከቻነት የዋሉትን ስነዘዴ፣ ጽንሰ ሃሳባዊና ንድፈ ሃሳባዊ ማዕቀፍችን ያስተዋውቃል፡፡ የቱለማ ኦሮሞዎችን የከበራ ማዕከላዊ ሥፍራዎችን ታሳቢ በማድረግ ምልከታ፣ ቃለ መጠይቅ፣ የተተኳሪ የቡድን ውይይት ለመረጃ መሰብሰቢያነት ውለዋል፡፡ ጥናቱ አይነታዊ የምርምር ስነዘዴዎችን የተከተለ ሲሆን ገላጭና ተንታኝ የአጠናን ስሌትን ተግባራዊ አድርጓል፡፡ ዘዴው የተመረጠበት ምክንያት የትዕምርቶቹን ተፈጥሯዊ ባህርያት፣ ከምንና እንዴት እንደተሰሩ፣ በገዲ ሥርዓት ውስጥ ያላቸውን ውክልናና ፍቺ እንዱሁም ሚና ለመግለጽ የሚረዲ በመሆኑ ነው፡፡ የተጠቀሱትን የጥናት መመሌከቻዎችና የምርምር ስነዘዳዎችን በመከተሌ የዋቃ (የፇጣሪና ተፇጥሮ) ትዕምርቶች እንዱሁም ቦኩ፣ ከሇቻ፣ ጫጩ፣ ጨላ የመሳሰለት የከበሩ ንዋያት ተተንትነዋል፡፡ በተካሄደው ትንታኔም እነዚህ የከበሩ ንዋያት ሥልጣንን፣ ማህበራዊ ደረጃን፣ ፆታን፣ የወንዴና ሴት እኩሌነትን፣ ማህበራዊ ፌትህን፣ እውነትና ቅዴስናን፣ መራባትንና የትውልድ መቀጠልን የሚወክለ ናቸው፡፡ የገዲ ሥርዓት በጊዛ የተገደበ ሰማዊ የሥሌጣን ሽግግር፣ የዳሞክራሲና የሰብዓዊ መብቶች እንዱሁም ስነምግባራዊ እሴቶች ሇሀገራችን የመንግሥት አስተዲዯር ጥሩ ተሞክሮ ሉሆኑ እንዯሚችለ በትንታኔው ታይቷል፡፡ የከበሩ ንዋያቱ ግጭትን ለማስወገዴ፣ እርቅ እና ሰሊምን (Araara fi naga’a) ሇማስፇን፣ ብቀሊን ፌፁማዊ ወዯሆነ ወንዴማማችነት በመቀየር ረገዴ መተኪያ የላሊቸው መሆናቸውም በጥናቱ ማጠቃለያና ግኝት ተረጋግጧሌ፡፡ የገዲ ሥርዓትና የዋቄፈና እምነት ከበራዎችን ይሌቁንም ዯግሞ የጉማ ሥርዓትን ከከሇቻና ጫጩ ውጪ ማሰብ አስቸጋሪ መሆኑንም የጥናቱ መዲረሻ አመላክቷል፡፡ ከቅርብ ጊዛ ወዱህ እየታየ ያለው ለውጥ ፈጣን በመሆኑ የከበሩ ንዋያቱ ባህሊዊ ይዘታቸው ሳይቀየር ተመዜግበው እንዱቀመጡና ሇቀጣዩ ትውሌዴ እንዱተሊሇፈ እራሱን የቻሇ ሙዙየም ቢ዗ጋጅሊቸው ሇትምህርታዊ አገሌግልትና ሇገቢ ማመንጫ ሉውለ እንዯሚችለም የጥናቱ ይሁንታ በምክረ ሃሳብ መሌክ ጠቁሟሌ፡፡ የጥናቱ ቁሌፌ ቃሊት፡- የቱለማ ኦሮሞ ገዳ ሥርዓት፣ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ የከበረ ንዋያት፣
  • Item
    በተማሪዎች የአማርኛ ትምህርት የማንበብና የመፃፍ ክሂሎች ላይ የመምህራን ቃላዊና ፅሁፋዊ ምጋቤምላሽ አቀራረብ ትንተና (በምስራቅ ጉራጌ ዞን ኬላ ወረዳ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በ9ኛ ክፍል ተማሪዎች ተተኳሪነት)
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2016) ደረጀ ሰለሞን; ዳዊት ፍሬህይወት (ዶ/ር)
    የዚህ ጥናት ዋና ዓላማ በተማሪዎች የአማርኛ ትምህርት የማንበብና የመጻፍ ክሂሎች ላየመምህራንን ቃላዊና ጽሁፋዊ ምጋቤምላሽ አቀራረብ መተንተን ነው፡፡ ተጠኝዎቹም በምስራቅጉራጌ ዞን ኬላ ወረዳ 2ኛ ትምህርት ቤቶች የሚያስተምሩ አምስት መምህራን ሲሆኑ በጠቅላይእና 70 ተማሪዎች በእጣ ናሙና ተወስደዋል፡፡ 55ቱ ተማሪዎች የጽሁፍ መጠይቁን በአግባቡሞልተው መልሰዋል፣ በመሆኑም በትንተና ክፍሉ የተካተቱት እነዙህ ብቻ ናቸው፡፡ የጥናቱንዓላማ ለማሳካትም በሰነድ ፍተሻ፣ በምልከታ፣ በቃለመጠይቅና በጽሁፌ መጠይቅ መረጃዎችተሰብስበው፣ በአይነታዊ እና በመጠናዊ መተንተኛ ዘዴዎች በአፅንኦት ተተንትነዋል፡፡ የጥናቱግኝትም የቋንቋ መምህራን የማንበብና መጻፍ ክሂሎችን ሲያስተምሩ ሁሉንም የምጋቤምላሽዓይነቶች እየቀያየሩ ወይም አንዱን ከአንዱ ጋር እያጣመሩ በሚገባ መጠቀም አለመቻላቸውን፣ብዙውን ጊዜ የግልና የብጤ (ጓደኛ) ምጋቤምላሾችን በመጠቀም ምጋቤምላሽ እንደማይሰጡ እናበምጋቤምላሽ አሰጣጥ ወቅት ማስረጃዎችን እንጂ ደጋፊ ምልክቶችን እንደማይጠቀሙ እናየመምህራን ምጋቤምላሽ አቀራረብ የተለያየ መሆኑን ጥናቱ አረጋግጧል፡፡ከጥናቱ መሰረታዊግኝቶች በመነሳት አስተያየቶችንማቅረብ የተቻለ ሲሆን የአማርኛ ቋንቋ መምህራን ለአራቱምየምጋቤምላሽ ዓይነቶች ትኩረት ሰጥተው ለተማሪዎች የሚገባቸውን ምጋቤምላሽ እኩል ሊባልበሚችል ደረጃ ቢሰጡ፣ መምህራን ለገምጋሚ ምጋቤምላሽ ዓይነት ትኩረት በመስጠት ክፍልውስጥ ምጋቤምሊሻቸውን ማቅረብ ቢችሉ፣ ምጋቤምላሽ በሚሰጡበት ወቅት የመሰላቸትናየድካም ስሜት በአንዳንድ መምህራን የተስተዋለ ስለሆነ በይበልጥ የማንበብና የመጻፍክሂሎችን በሚያስተምሩበት ወቅት ድካማቸውን ሊያስወግድ የሚችሉ ዘዴዎችን ቢያመቻቹየሚሉት ቀርበዋል፡፡
  • Item
    በአዲሱ የ9ኛ እና የ10ኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ውስጥ የቀረቡት የጽሕፈት ክሂል ትምህርት ይዘቶች አደረጃጃት ንጽጽራዊ ግምገማ
    (Addis Ababa University, 2016-09) ጀማል ደዋ; ዶ/ር ግርማ ገብሬ
    የዚህ ጥናት ዋና በአዲሱ የ9ኛእና የ10ኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ውስጥ የቀረቡት የጽሕፈት ክሂል ትምህርት ይዘቶች አደረጃጃት በንጽጽር መገምገም ነው፡፡ ጥናቱ ሶስት መሰረታዊ ጥያቄዎችን ለመመለስ ታስቦ የተዘጋጀ ነው፡፡ ይህንን አላማ ለማሳካት የተመረጠው ገላጭ የምርምር ንድፍ ሲሆን የተገኙት መረጃዎች ተሰብስበው በመጠናዊና በአይነታዊ የምርምር ዘዴዎች ተተንትነዋል፡፡ ለዚህ ጥናት የተመረጡት የዘጠነኛ እና የአስረኛ (9ኛ-10ኛ) የክፍል ደረጃ መማሪያ መጻሕፍት በ2015ዓ.ም ለሙከራ ስራ ላይ የዋለትን መማሪያ መጻሕፍት በአላማ ተኮር የንሞና ዘዴ ተመርጠዋል፡፡ በእነዚህ ሁለት የክፍል ደረጃዎች ውስጥ መማሪያ መጻሕፍትን በማዘጋጀት ላይ ከሚገኙት ውስጥ አንድ የመማሪያ መጻሕፍት አዘጋጅ ቃለ መጠይቅ ተደረጓል፡፡ ጥናቱ ለማካሄድ በሁለቱም መማሪያ መጻሕፍት የተለያዩ ምዕራፍችና ገፆች ውስጥ የሚገኙትን የመፃፍ ክሂል ትምህርት ይዘቶች በሰነድ ፍተሻ ተለይተው ተሰብስበዋል፡፡ ለጥናቱ የሚያስፈልጉት መረጃዎች ከተሰበሰቡ በኃላ በይዘት አደረጃጀት መርሆች ትንትናና የአተናተን ዘዴ መሰረት በመማሪያ መጻሕፍት ውስጥ ያሉትና የሌሉት ይዘቶቹ በአይነት ተለይተው ተተንትነዋል፡፡ በተገኘው ውጤት መሰረት በሁለቱም መማሪያ መጻሕፍት ውስጥ የተካተቱት የጽሕፈት ክሂል ትምህርት ይዘቶች ብዛት 21 ሲሆን አማካኝ የድግግሞሽ መጠናቸውም 87.5% ሆኖ ተከታታይነታቸውን ጠብቀውና ስፋት ጥልቀታቸውን እየጨመሩ የመሄድ ሁኔታ ታይቶባቸዋል፡፡ ነገር ግን በሁለቱም መማሪያ መጻሕፍት ውስጥ 29.8% የሚደርሱ የመፃፍ ክሂል ትምህርት ይዘቶች አንዴ ብቻ ቀርበው ሳይደጋገሙ መኖራቸው ለማየት ተችሏል፡፡ ከተደራጁት 21 የየጽሕፈት ክሂል ትምህርት ይዘቶች ውስጥ 9ኙ ብቻ ተለጣጣቂነት ሲቀርቡ የተቀሩት 12ዎቹ ደግሞ ተለጣጣቂነታቸው ሳይጠብቁ የቀረቡ መሆናቸውን ጥናቱ አመላክቷል፡፡ በጥናቱ ውጤት መሰረትም በመማሪያ መጻሕፍት ውስጥ የሚቀርቡ የመፃፍ ክሂል ትምህርት ይዘቶች በሁለም የእርከኑ መጻሕፍት ውስጥ ተለጣጣቂነት/ ቀጣይነት/ እንዲኖራቸው ለማድረግ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እና እንደ አስፈሊጊቱ የተማሪዎች ዳራ መሰረት በማድረግ የጽሕፈት ክሂል ትምህርት ይዘቶች ከዝርዝር ወደ አጠቃላይና ከአጠቃላይ ወደ ዝርዝር ስልት አደረጃጀት አመጣጥኖ ማቅረብ ወደ አንድ ስልት ብቻ አለማመዘን የሚሉት በመፍትሔነት ተጠቁሟል፡፡
  • Item
    የመርሐ ቤቴ ልጃገረዶች የፋሲካ ጨዋታ ክዋኔ እና ፋይዳ
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2023-11) ታደሰ አዳነ; የወንድወሰን አውላቸው (ዶ.ር)
    ይህ ጥናት በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሰሜን ሸዋ ዞን፣ በመርሐ ቤቴ ወረዳ የፋሲካ በዓልን መሰረት በማድረግ በሚከበረው የልጃገረዶች ባህላዊ የፋሲካ ጨዋታ ክዋኔ እና ፋይዳ ላይ ትኩረት ያደረገ ሲሆን ይህን ጥናት ለመስራት ምክንያት ከሆኑት ምክንያቶች መካከል አንደኛ የመርሐ ቤቴ ልጃገረዶች የፋሲካ ጨዋታ እየደረሰበት ካለው የመደብዘዝና የመጥፋት ስጋት ለመታደግ የየጨዋታዎቹን ክዋኔና ፋይዳ ሰንዶ የማቆየት ፍላጎት ሲሆን፣ ሌላው ደግሞ ባደረግሁት የቀደምት ጥናቶች ዳሰሳ በዚህ ርዕሰ ጉዳይ የተሰሩ ጥናቶች ባለማግኘቴ ይህን ክፍተት ለመሙላት በማሰብ ነው፡፡ የጥናቱ ዋና ዓላማ “የመርሐ ቤቴ ልጃገረዶች የፋሲካ ጨዋታን አከዋወንና ፋይዳ መመርመር” ነው፡፡ ይህን ዓላማ ከግብ ለማድረስ በወረዳው የሚከወነው የልጃገረዶች የፋሲካ ጨዋታ ታሪካዊ አጀማመር መነሻ ምክንያቶች ምን ምን ናቸው? ስንት አይነት አና ምን ምን ዓይነት ጨዋታዎች ይከወናሉ? በወረዳው የሚከወነው የፋሲካ ጨዋታ ክዋኔ ሂደት ምን ይመስላል? የፋሲካ ጨዋታ ለተጠኝው ማህበረሰብ ምን ፋይዳ አለው? በጨዋታዎቹ ክወኔ ቀጣይነትና ይዘት ላይ ምን ዓይነት ስጋቶች ይስተዋላሉ? የሚሉ መሰረታዊ የምርምር ጥያቄዎች ተዘጋጅተው ምላሽ አግኝተዋል። ጥያቄዎቹን ለመመለስና የጥናቱን ዓላማ ለማሳካት የመርሐ ቤቴ ወረዳን ይወክላሉ ተብለው ከተመረጡት ከዓለም ከተማ፣ ከአፈዘዝ በርቃቶ፣ ከግሬት ወቸዋርኝ፣ ከአገሪት ቁምአምባ እና ሰባጌ ሃሮገንዳ ቀበሌዎች ስለጨዋታው ታሪክ ያውቃሉ ከተባሉ የሃገር ሽማግሌዎች፣ ከሃይማኖት አባቶች፣ ተጫውተው ካሳለፉ እናቶች፣ ከጨዋታው ተሳታፊ ልጃገረዶችና ወጣት ወንዶች እና ከባህልና ቱሪዝም ባለሙያዎች በአጠቃላይ ከአርባ አራት መረጃ አቀባዮች በምልከታ፣ በቃለ መጠይቅና በተተኳሪ የቡድን ውይይት መረጃዎች ተሰብስበዋል፡፡ የጥናቱን ቦታ እና መረጃ ሰጭዎች ለመምረጥ የዓላማ ተኮር የናሙና አመራረጥ ዘዴ ተግባራዊ የተደረገ ሲሆን መቅረፀ ድምፅ፣ የእጅ ስልክ፣ የቪዲዮና ፎቶ ካሜራና ማስታወሻ ደብተር መረጃ ለመሰብሰብ ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡ ከጥናቱ ጋር ተዛማጅነት ያላቸውና ጥናቱ የተነሳበትን ዋና ጉዳይ የሚያጠናክሩ ማጣቀሻዎች፣ ዋቢ ጽሑፎች፣ ቀደምት ተዛማጅ ጥናቶች ካዕላይ የመረጃ ምንጮች ከአብያተ መጻሕፍና ከኤሌክትሮኒክስ የመረጃ መረብ በንባብ ተቃኝተዋል፡፡ በዚህ መሰረት ስለርእሰ ጉዳዩ አስረጅ የሆኑ ጽንሰ ሃሳቦችና ቀደምት ጥናቶች ተዳስሰዋል፡፡ ጥናቱ አይነታዊ እንደመሆኑ መጠን በምልከታና በቃለ መጠይቅ የተሰበሰበው መረጃ በአግባቡ ተደራጅቶ ገላጭ የትንተና ዘዴን በመጠቀም ተተንትኗል፡፡ ለመረጃ ትንተና የክዋኔያዊና ተግባራዊ ንድፈ ሃሳቦች አገልግለዋል፡፡ የመርሐ ቤቴ ልጃገረዶች የፋሲካ ጨዋታ ታሪካዊ ዳራው/መነሻው/ የክርስትና ሃይማኖት እንደሆነና ከትንሳኤ እስከ ዳግም ትንሳኤ ድረስ አንድ ሳምንት በሚቆየው በዚህ ሁነት ልጃገረዶች ቀደም ብለው በሁለት መንገድ ቅድም ዝግጅት በማድረግ ከጫና ነጻ ሆነው በጨዋታው ላይ እንደሚሳተፉ እና አስር ዓይነት ጨዋታዎች ባህሉ የሚፈቅደውን ህግ በመከተል በቡድን እንደሚከውኑ ጥናቱ አሳይቷል፡፡ ጨዋታው ማህበራዊ መስተጋብርን በማጠናከር፣ ባህልና ሃይማኖትን በማስቀጠል፣ ወጣቶች በባህላቸውና በማንነታቸው እንዲኮሩ በማድረግ፣ አካላዊና ሥነልቡናዊ ጥንካሬአቸውን በማዳበር፣ በራስ መተማመናቸውን በማጎልበትና ሃሳባቸውን በነጻነት እንዲገልጹ በማድረግ በኩል ከፍተኛ ማህበራዊ፣ ሥነለቡናዊና አካላዊ ፋይዳዎች ቢኖሩትም በውስጣዊና ውጫዊ ችግሮች ምክንያት ስጋት እንደተጋረጠበት የጥናቱ ውጤት አመላክቷል፡፡ ከዚህ በመነሳትም የአካባቢው ማህበረሰብና የሚመለከታቸው አካላት የጨዋታውን ፋይዳ በመገንዘብ ሃላፊነታቸውን ቢወጡ፤ በማህበራዊ፣ ሥነ ለልቡናዊና ስፖርታዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩሩ ተቋማትና የመስኩ ምሁራን ከዚህ ጥናት በበለጠ ሰፊ ጊዜና በጀት መድበው በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚታዩ ጉዳዮችን አጥንተው የሚያበረክተውን ፋይዳ ቢያሳውቁ፤ ጨዋታው እንዲታወቅና ጎብኝዎች እንዲኖሩት ለማድረግ ባህልና ቱሪዝም፣ መገናኛ ብዙኀንና የሚመለከታቸው የመንግስትና የግል ተቋማት ትኩረት ሰጥተው በጋራ ቢሰሩ የሚሉ የይሁንታ ሃሳቦች ተጠቁመዋል፡፡
  • Item
    አፋቸውን በኦሮምኛ ቋንቋ የፈቱ ተማሪዎች በአማርኛ ቋንቋ፣ ክፍለ ጊዜ ያላቸው የክፍል ውስጥ ተሳትፎ እና የውጤት ተዛምዶ (በጊንጪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የ9ኛ ክፍል ተማሪዎች ተተኳሪነት)
    (Addis Ababa University, 2023) በላቸው ማንደፍሮ; ዶ/ር ጌታቸው አዱኛ
    የዚህ ጥናት ዋና ዓላማ በኦሮምኛ ቋንቋ አፋቸውን የፈቱ ተማሪዎች በአማርኛ ቋንቋ ክፍለ ጊዜ በሚያደርጉት የክፍል ውስጥ ተሳትፎና በአማርኛ ቋንቋ ውጤታቸው መካከል ያለውን ተዛምዶ መመርመር ነው፡፡ ይህን ዓላማ ለማሳካት ተዛምዷዊ የጥናት ንድፍን ተግባራዊ ተደርጓል፡፡ የጥናቱ ተሳታፊዎች በጊንጪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተማሩ 48 የዘጠነኛ ከፍል ተማሪዎች ናቸው፡፡ ትምህርት ቤቱ በአመቺ የንሞና ስልት የተመረጠ ሲሆን ተማሪዎች ደግሞ በጠቅላይ የንሞና ስልት በጥናቱ ተካተዋል፡፡ ከ48 ተማሪዎች በአማርኛ ቋንቋ ክፍለ ጊዜ ያላቸውን ተሳትፎ በምልከታና በጽሑፍ መጠይቅ እንዲሁም የአማርኛ ቋንቋ ውጤታቸውን ደግሞ በአማርኛ ቋንቋ ፈተና ተሰብስቧል፡፡ መረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያዎቹ (የጽሑፍ መጠይቁና የአማርኛ ቋንቋ ፈተናው) መረጃ ለመሰብሰቢያነት ከማገልገላቸው በፊት በፍተሻ ጥናት (Pilot Study) መረጃዎች ተሰብስበው፣ መረጃዎች በክሮንባኽ አልፋ ተፈትሸው የተገኘው ውጤት ከ0.7 በላይ በመሆናቸው (አስተማማኝ በመሆናቸው) ለዋናው ጥናት መረጃ መሰብሰቢያነት አገልግለዋል፡፡ ከዚያም ጥናቱ ይዟቸው የተነሳውን መሰረታዊ ጥያቄዎች ለመመለስ ፒርሰን የተዛምዶ መወሰኛ፣ የቀላል ድህረታዊ እና የነጻ ናሙና ቲቴስት ስሌቶች አማካይነት የተሰበሰቡ መረጃዎች ተተንትነዋል፡፡ በትንተናው ውጤትም በአማርኛ ቋንቋ ክፍለጊዜ የክፍል ውስጥ ተሳትፎ እና በአማርኛ ቋንቋ ውጤት መካከል ጉልህ የሆነ አዎንታዊ ተዛምዶ (r=.642፣ P<.01፣ ባለሁለት ጫፍ) እንዳለ እና የተዛምዶ ደረጃውም ከፍተኛ እንደሆነ የፒርሰን የተዛምዶ መወሰኛ ፍተሻው አሳይቷል፡፡ ነጻ ተለዋዋጩ (በአማርኛ ቋንቋ ክፍለጊዜ የክፍል ውስጥ ተሳትፎ) ጥገኛ ተለዋዋጩን (የአማርኛ ቋንቋ ውጤትን) 41.2% እንደሚገልጸው የቀላል ድህረታዊ ትንታኔው ውጤት (R2 = .412፣  = .642፣ F (1፣ 47) = 32.267፣ t = 5.680፣ p = .000) አሳይቷል፡፡ የወንድና የሴት ተማሪዎች የክፍል ውስጥ ተሳትፎ አማካይ ውጤቶች መካከል ልዩነት አለመኖሩን የነጻ ናሙና ቲ-ቴስት ትንታኔው (t (46) = .776, p = 0.442) ያሳዬ ሲሆን የአማርኛ ቋንቋ ውጤታቸው መካከል ያለውን ልዩነት ተፈትሾ የሴትና የወንድ ተማሪዎች በአማርኛ ቋንቋ ትምህርት አማካይ ውጤቶች መካከል ጉልህ ልዩነት (t (46) = .301, p = .765) አለመኖሩን በጥናቱ ተረጋግጧል፡፡ ከጥናቱ ግኝት በመነሳት መምህራን የተማሪዎችን የክፍል ውስጥ ተሳትፎ እንዲጨምር የበኩላቸውን አስተዋጽዖ ቢያበረክቱ፤ መምህራን የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል ተማሪዎችም እንዲሳተፉ በማነቃቃትና አሳታፊ ማስተማሪያ ዘዴዎችን በመከተል ተሳትፏቸውን እንዲጨምር ቢያደርጉ፤ የክፍል ውስጥ ተሳትፎ እና የትምህርት ውጤት ካላቸው ከፍተኛ ዝምድና አንጻር ተማሪዎች የክፍል ውስጥ ተሳትፏቸውን በማሳደግ ውጤታቸውን ማሳደግ እንዲችሉ የሥርዓተ ትምህርት አዘጋጆች መማሪያ መጻሕፍትንና የመምህር መምሪያዎችን ሲያዘጋጁ ተማሪዎች እንዲሳተፉ ምቹ የሆነና የሚያበረታታ እንዲሆን ትኩረት ቢያደርጉ እና በሁለቱም ጾታዎች ያለው የተሳትፎ ምጥጥን ተጠናክሮ እንዲቀጥል ቢደረግ የሚሉ አስተያየቶች በአጥኚው ቀርበዋል
  • Item
    የወላይትኛ አፈ-ፈት ተማሪዎች በአማርኛ ድርሰት ሲጽፉ የሚፈፅሟቸው ዋና ዋና የስህተት ዓይነቶች እና የስህተት ምንጮች ትንተና፡ በ10ኛ ክፍል ተማሪዎች ተተኳሪነት
    (Addis Ababa University, 2023-09) እናትነሽ ጌትነት; አክሊሉ ይልማ (ተባባሪ ፕሮፌሰር)
    የዚህ ጥናት አብይ ዓላማ በወላይትኛ ቋንቋ አፋቸውን የፈቱ ተማሪዎች በአማርኛ ድርሰት ሲጽፉ የሚፈጽሟቸው ስህተቶችና የስህተት ምንጮችን በመለየት ስህተቶችን መተንተን ነው፡፡ ጥናቱም አይነታዊና መጠናዊ የምርምር ዘዴን የተከተለ ሲሆን፣ ለአቀራራቡ ገላጭ ሰልት ተግባራዊ ተደርጓል፡፡ መጠናዊ የምርምር ዘዴ ተግባራዊ የተደረገው በተማሪዎች ድርሰት ውስጥ የታዩ የስህተቶቹን ብዛት እና የድግግሞሽ መጠን ለመለየትና ለመተንተን ነው፡፡ የጥናቱ ተሳታፊዎች በ2015 ዓ.ም. በወላይታ ዞን በዳሞት ወይዴ ወረዳ በዴሳ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ይማሩ የነበሩ በወላይትኛ አፈ-ፈት የሆኑ የ10ኛ ክፍል 55 ተማሪዎች ናቸው፡፡ የጥናቱ መረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያዎች በክፍል ውስጥ በተማሪዎች የተጻፈ ድርሰት፣ የሰነድ ፍተሻ፣ የጽሁፍ መጠይቅ እና ቃለመጠይቅ ሲሆኑ፣ መረጃዎች በገላጭ ስልት ተተንትነዋል፡፡ የጥናቱ ውጤት በተማሪዎች ድርሰት ውስጥ ከታዩ ከቋንቋ አጠቃቀም፣ ከቋንቋ አወቃቀር፣ ከስርዓተ ነጥብ አጠቃቀም እና ስርዝ ድልዝ ስህተቶች ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ የስህተት ምንጮች የአፍ መፍቻ ቋንቋ ጣልቃ ገብነት፣ የውስጠ-ቋንቋ ተጽዕኖ፣ የመማሪያ ክፍል ውስጥ አውድ (የመማር ማስተማር ሂደትና የማስተማሪያ መሳሪያዎች) እና ማህበራዊና ስነልቦናዊ ተጽዕኖ መሆናቸው ተረጋግጧል፡፡ ስለሆነም ባለድርሻ አካላት ሁሉ ከጥናቱ ውጤት በመነሳት በአማርኛ ቋንቋ ኢ-አፈ-ፈት የሆኑ ተማሪዎች የተለያዩ የክፍል ውስጥ ተግባራትን በማዘጋጀት ማስተማር ይጠይቃል፡፡
  • Item
    በ9ኛ ክፍል ተማሪዎች የመፃፍ ክሂል ችሎታ ከፆታ አንፃር ንፅፅራዊ ጥናት (በእኖር ኤነር መገር ወረዳ የመገር ወይራ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተተኳሪነት)
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2023-10) አሚናት መሀመድ; ግርማ ገብሬ (ድ/ር)
    የዚህ ጥናታዊ ጽሁፍአላማ በሴትና በወንድ ተማሪዎች መካከልሀሳባቸውን በጽሁፍ ከመግለጽ አንጻር የተሻሉት የትኞቹ እንደሆኑ ማነጻጸር ነው። በመሆኑም በአማርኛ ቋንቋ ድርሰት የመጻፍ ክሂላቸውን ለማነጻጸር ያስችል ዘንድ መጠናዊ እና አይነታዊ የምርምር ዘዴ በሱ ስር የሚመደበው ገላጭ የአጠናን ዘዴን በመጠቀም እንዱሁም ከመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴዎች ደግሞ የችሎታ መለኪያ ፈተናና የጽሁፍ መጠይቅን በመጠቀም የተገኘውን መረጃ ተንትናለች። ተጠኝ ተማሪዎችን በእድል ሰጪ የናሙና አወሳሰድ ዘድን በመጠቀም በጉራጌ ዞን በእኖር ኤነር መገር ወረዳ በመገር ወይራ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2015 አ.ም ለናሙናነት በተመረጡ ሴት 47 ወንድ 39 በድምሩ 86 ተጠኝ ተማሪዎች እና ሁለት ሴት ሶስት ውንድ በድምሩ አምስት መምህራን ሲካተቱ የችሎታ መለኪያ ፈተና ድርሰት ሲጽፍ የጻፉት ዴርሰት ተነባቢነት የጎደለው በመሆኑ ሴት አንድ (1)ወንድ (3)ሶስት በድምሩ (4) ተማሪዎች በዚህ ጥናት ያልተካተቱ ሲሆኑ ድርሰቱን በትክክል የጻፉ ተማሪዎች ሴት 46 ወንድ36 በድምሩ 82 ተማሪውች በችሎታ መለኪያ ፈተናው የተካተቱ ሲሆኑ የጽሁፍ መጠይቁን በትክክል ያልሞለት ድግሞ ወንድ 3 ተማሪዎች በጥናቱ ያልተካተቱ ሲሆኑ በአጠቃሊይ ሴት 47 ወንድ 36 ድምር 83 ተማሪዎች በጽሁፍ መጠይቁ የተካቱ ናቸው። በመሆኑም ሁለቱን የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴዎች በመጠቀም የተፈለገው መረጃ ተሰብስቧል ማለት ነው። የችሎታ መለኪያ ፈተናውን ለተከታታይ ለሶስት ዙር ድርሰት በማጻፍየመጀመሪያውን በመጣልና በቀጣይ ሁለት ተከታታይ የጻፉትን በመውሰድና በሶስት አራሚዎች በማሳረም የተገኘውን ውጤት አስተማማኝነቱን ለማረጋገጥ በቲ ቴስት ስላት ተሰሌቶ የቲ ዋጋ 6.241 አስተማማኝ ሲሆን የፒ ዋጋ ደግሞ 0.000 ልዩነት መኖሩን ሲያመለክት የሜን ድፈረንስ ውጤት ደግሞ 12.104 በመሆኑ ሴት ተማሪዎች ከወንድ ተማሪዎች የላቀ ወጤት ማምጣታቸውን እና ሀሳባቸውን በጽሁፍ ከመግለጽ አንጻር የተሻለ መሆናቸውን ከተገኘው ውጤት ማወቅ እና መረዳት ተችሏል። ሌላው ተማሪዎች የጽሁፍ መጠይቅ የቀረበላቸው 23 ዝግ ጥያቄ (በReliabilityTests) ተሰልቶ የተገኘው ውጤት (0.871) በመሆኑ ትክክለኛነቱ ተረጋግጧል። ከመጠይቁ የተገኘው የመምህራን ውጤት በፐርሰንት እና በአሀዝ ተሰልቶ ሲቀመጥ ከተማሪዎች የተገኘው ምሊሽ ደግሞ በአምስት ዋና ዋና የመጠይቅ ይዘቶች ሲገመገሙ በአራቱ የመመዘኛ መሰፈርቶች ሴት ተማሪዎች ከወንድ ተማሪዎች የተሻለ ሆነው ሲገኙ ከቋንቋ አጠቃቁም አንጻር በተሰላው የቲ ቴስት ወጤት 1.671 ሲሆን የፒ ዋጋ ደግሞ 0.099 አንሶ በመገኘቱ በሁለቱ ጾታዎች መካከል ከግምት የሚገባ ልዩነት አለመኖሩን ያመላክታል። አንጻራዊ በሆነ መልኩ ሲታይ በችሎታ መለኪያ ፈተናውም ሆነ በጽሁፍ መጠይቁ የተገኘው ውጤት የሚያሳየው ሴት ተማሪዎች ከወንድተማሪዎች በተሻለ ሁኔታ ሀሳባቸውን መግለጽ እንደሚችሉከተገኘው መረጃ መረዳት ተችሏል
  • Item
    በኦሮምኛ ቋንቋ አፋቸውን የፈቱ ተማሪዎች የአማርኛ ቃላትን በሚማሩበት ጊዜ የትኞቹን ብልሃቶች በተደጋጋሚ አብዝተው እንደሚጠቀሙ መለየት (በአስረኛ ክፍል ተማሪዎች ተተኳሪነት)
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2022-07) ያሲን አደም; ዳዊት ፍሬህይወት (ዶ/ር)
    የዚህ ጥናት ዋና አላማ በኦሮምኛ ቋንቋ አፋቸውን የፈቱ ተማሪዎች የአማርኛ ቃላትን በሚማሩበት ጊዜ የትኞቹን ብልሃቶች በተደጋጋሚ አዘውትረው እንደሚጠቀሙ መመርመር ነው፡፡ ተሳታፊዎች በኦሮሚያ ብሔረሰብ ልዩ ዞን በሩፍሴ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2015 ዓ.ም በመማር ላይ ያሉ የአስረኛ ክፍል ተማሪዎች በአመች ንሞና ዘዴ ተመርጠዋል፡፡ ጥናቱም ገላጭ የምርምር ስልትን የተከተለ ነው፡፡ በጽሁፍ መጠይቅና በቃለ መጠይቅ አማካኝነት የጥናቱ መረጃዎች ተሰብስበዋል፡፡ እነዚህ መረጃዎችም በአይነታዊና መጠናዊ የመረጃ መተንተኛ ስልቶች ተተንትነዋል፡፡ የጥናቱ ውጤት እንደሚያሳየው በኦሮምኛ ቋንቋ አፋቸውን የፈቱ ተማሪዎች የአማርኛ ቃላትን በሚማሩበት ጊዜ ጥቅል አካካሽ ብልሃቶችን 101(144.3%) ያህልጊዜ በመደጋገም ሲጠቀሙ፣ ሌሎቹን ብልሃቶች በተደጋጋሚ አዘውተረው እንደማይጠቀሙባቸው አመላክቷል፡፡ ለዚህ ተግባር እንደምክናየት የቀረቡት የተማሪዎቹ የትውስታ፣ የአዕምሮታዊ፣ የልዕለ አዕምሮታዊ፣ስሜትነክና ማህበራዊ ብልሃቶችን ሲገለገሉ ሁልጊዜ እንደማይጠቀሙበት ሲያሳየን በአንጻሩ ደግሞ የአካካሽ ብልሃት አጠቃቀማቸው በብቃት ላይ የተመሰረተ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ከዚህም በመነሳት ተጠኚ ተማሪዎች በተደጋጋሚ አብዝተው የሚጠቀሙት አካካሽ ብልሃቶችን ሲሆን ሌሎቹን ብልሃቶች ግን አዘውትረው እንደማይጠቀሙባቸው ከሚል መደምደሚያ ላይ ተደርሷል፡፡ የአማርኛ ቋንቋ መማርያ መጽሐፍት አዘጋጆች የቃላት መማር ብልሃቶችን በተመለከተ ስነ-ዘዴዎችን ቀርጸው እንደ አንድ የቃላት ትምህርት ማቅረቢያ ዘዴ ቢጠቀሙበት፣ የቋንቋ መምህራን ተማሪዎችን በራሳቸው ጥረት እንዲሳተፉ ቃላትን የመማር መንገድ ቢያመቻቹላቸውና ክትትል ቢያደርጉላቸው የሚሉ የመፍትሄ ሃሳቦች ቀርበዋል፡፡
  • Item
    ለ7ኛ እና ለ8ኛ ክፍል በተዘጋጁት የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መጻሕፍትና የመምህሩ መምሪያ ውስጥ የተካተቱ የሰዋስው ትምህርት ይዘቶች አቀራረብ እና አደረጃጀት ከመርሀ-ትምህርቶቹ ጋር ያላቸውን ተጣጥሞሽ መፈተሽ
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2022-08) ደስታ አበጋዝ; ዶ/ር ዳዊት ፍሬህይወት
    የዚህ ጥናት ዋና አላማ በ2014 ዓ.ም. በ ሲዳማ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት አማካኝነት በታተሙት የ7ኛ እና የ8ኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መጻሕፍትና የመምህሩ መምሪያ ውስጥ የተካተቱ የሰዋስው ትምህርት ይዘቶች አቀራረብ እና አላረጃጀት ከመርሀ-ትምህርቶቹ ጋር ያሊቸውን ተጣጥሞሽ መፈተሸ ነው፡፡ የጥናቱን ዓላማ ለማሳካት ሰነድ ፍተሻ የጥናቱ መረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያ በመሆኑ የ7ኛ እና የ8ኛ ክፍል መማሪያ መጻህፍትና የመምህሩ መምሪያ እንዲሁም ለደረጃው የተዘጋጁ መርሀ-ትምህርቶች በመረጃ ምንጭነት አገልግለዋል፡፡ ጥናቱም ቅይጥ የምርምር ዘዴን በመጠቀም በሰነድ ፌተሻ የተገኙ መረጃዎች በክለሳ ድርሳን ከተነሱ ንዴፈ-ሃሳቦች አኳያ በገላጭ የምርምር ስልት ተተንትነዋል፡፡በተተኳሪዎቹ መጻህፌትና የመምህሩ መምሪያ ውስጥ ያለ የሰዋስው ይዘቶች በመርሀ-ትምህርቱ ውስጥ ከተካተቱት ይዘቶች ጋር በአብዛኛው የሚጣጣሙ መሆናቸውን ከሰነድ ፍተሻው ለማረጋገጥ ተችሎል፡፡ በተተኳሪዎቹ ሰነድች ውስጥ የተካተቱ የሰዋስው ትምህርት ይዘቶች ከሰዋስው ትምህርት አቀራረብ መርሆዎች አኳያ ሲፈተሹ በአብዛኛው ግልጽ፣ ትክክለኛ፣ተገቢነትና ተመጣጣኝነት ያላቸው ቢሆኑም አልፎ አልፎ ግን ግልጽነት የጎደላቸው ማብራሪያዎች፣ ትእዛዞች፣ ምሳሌዎችና መልመጃዎች፤ ስህተት ያለባቸው የሰዋስው ይዘቶች፤ ከክፍል ደረጃው በላይ የሆኑ የሰዋስው ትምህርት ይዘቶች እና ያልተመጣጠኑ ንኡሳን ይዘቶች እንዳሉ በተደረገው ሰነድ ፍተሻ ለማረጋገጥ ተችሎል፡፡ በተተኳሪዎቹ ሰነድች ውስጥ የተካተቱ የሰዋስው ትምህርት ይዘቶችና አደረጃጀት በአብዛኛው ተከታታይነትና ተለጣጣቂነት ያላቸው ሲሆኑ አንዳንድ ይዘቶች ግን ምንም ስፋትና ጥልቀታቸው ሳይጨምር የተደገሙ መሆናቸው በደካማ ጎን የሚያይ ነው፡፡ እንዲሁም ከአጠቃላይ ወደ ዝርዝርና ከዝርዝር ወደ አጠቃላይ አደረጃጀትን የተከተለ ቢሆንም በአመዛኙ ከዝርዝር ወደ አጠቃላይ አደረጃጀት ጎልቶ ታይቶባቸዋል፡፡ በተጨማሪም የ7ኛና የ8ኛ ክፍሌ መማሪያ መጻህፍትና የመምህሩ መምሪያ ውስጥ የተካተቱ የሰዋስው ትምህርት ይዘቶች አቀራረብና አደረጃጀት በአብዛኛው በመርሀ-ትምህርቱ ላይ የተመሠረቱ ቢሆንም የተወሰኑ የሰዋስው ይዘቶች አቀራረብና አደረጃጀት ዳግሞ በሚገባ መርሀትምህርቱ ላይ ተመስርተው ያለመቅረባቸውን ከተደረገው ሰነድ ፍተሻ ለማረጋገጥ ተችሎል፡፡ ይህንን መነሻ በማድረግም በጥናቱ ማጠናቀቂያ ላይ ክፍተቱን ለመሙላት ያስችላሉ የተባለ አስተያየቶች ተሰጥተዋል፡፡
  • Item
    በክስታኔ ጉራጌ ቋንቋ አፈ-ፈት የሆኑ ተማሪዎች በአማርኛ ቋንቋ ጽሐፍ ሲጽፉ የሚፈጽሟቸው ስህተቶች ትንተና (በ9ኛ ክፌል ተተኳሪነት)
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2023-09) ወጋየሁ አሰፋ; (ዶ/ር) ሙለሰው አስራቴ
    የዚህ ጥናት አብይ አላማ በጢያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሚማሩ የክስታኔ ጉራጌ ቋንቋ አፌ-ፈት የሆኑ የ9ኛ ክፍል ተማሪዎች በአማርኛ ቋንቋ ጽሐፍ በሚፅፈበት ጊዜ የሚፈፅሟቸውን ዋና ዋና የስህተት አይነቶች እና የስህተት ምንጮች መለየት ነው፡፡ ይህንም አላማ ከግብ ለማድረስ አጥኚዋ የተጠቀመችው ቅይጥ የምርምር ዘዴን ነው፡፡ ጥናቱ የተካሄደው በጢያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሲሆን የተመረጠውም በአመቺ የናሙና ዘዴ ነው፡፡ በትምህርት ቤቱ ከሚገኙ የክስታኔ ጉራጌ ቋንቋ አፈት ከሆኑ የ9ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል 60 ተማሪዎችን በእኩል እድል ሰጪ የናሙና ዘዴ በመምረጥና ሶስት የ9ኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መምህራንን በጠቅላይ የንሞና ዘዴ በመምረጥ አስፈላጊው መረጃ ተሰብስቧል፡፡ መረጃው የተሰበሰበውም ተጠኚ ተማሪዎችን በሁለት ዙር ጽሐፍ በማጻፍና የጽሐፍ መጠይቅ በማስሞላት እንዲሁም መምህራንን ቃሇለ መጠይቅ በማስሞላት ሲሆን ገላጭ የትንተና ዘዴን በመከተል ትንተናው ተሰርቷል፡፡ ተማሪዎቹ የፃፋቸውን ጽሁፍች በሶስት መምህራን በማሳረም የፈፀሟቸውን ዋና ዋና የስህተት አይነቶችን መለየት ተችላል፡፡ በመረጃ ትንተና ውጤቱ መሰረትም ዋና ዋና የስህተት በአይነቶቹ የሆሄያት አጠቃቀም ስህተት፣ የቃላት ዴግግሞሽ ብዛት፣ የስርዓተ-ነጥብ አጠቃቀም ስህተት፣ የቃላት ድረታ ብዛት፣ የሰዋስው ስህተት እንዲሁም የሀሳብ አገላለፅ ችግር መሆናቸው ተመልክቷል፡፡ በመረጃ ትንተና ውጤቱ መሰረትም የስህተት ድግግሞሹን ስንመለከት የቃላት ድግግሞሽ 4.87፣ የቃላት ድረታ 3.84፣ የሰዋስው ስህተት 1.97፣ የስርተ-ነጥብ አጠቃቀም ስህተት 4.27፣ የሆሄያት አጠቃቀም ስህተት 9.07፣ እንዲሁም የሀሳብ አገላለፅ ስህተት 1.73 መሆኑን የጥናቱ ውጤት ያሳያል፡፡ የጥናቱን ውጤት መሰረት በማድረግም መምህራን፣ ተማሪዎቻቸው ፉደላትን በስርዓት እንዱለዩና ፅህፈትን ደጋግመው እንዲለማመዱ ቢያደርጉ፤ መርሐ ትምህርት፣ አዘጋጆች መርሐ ትምህርቱን እንደገና ቢገመግሙት፤ መጽሀፍ አዘጋጆች፣ በመፅሀፍ ውስጥ የተካተቱትን የፅህፈት ትምህርት ይዘቶችን እንደገና ቢገመግሟቸው፤ መልካም ነው የሚል አስተያየቶች ተጠቁመዋል፡፡
  • Item
    በመደበኛው እና በማታው መርሃ ግብር የሚያስተምሩ የአማርኛ ቋንቋ መምህራን የማንበብ ክሂል ትምህርት የክፍል ውስጥ አተገባበር ንጽጽራዊ ጥናት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በተመረጡ የመንግስት ትምህርት ቤቶች (በ9ኛ ክፍል ተተኳሪነት)
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርሰቲ, 2023-09) ዝናሽ ብርሃኑ; ዶ/ር ጌታቸው እንዳላማው
    የዚህ ጥናት አብይ አላማ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሚገኙ የመንግስት ትምህርት ቤቶች በመደበኛው እና በማታው መርሃ ግብር የሚያስተምሩ መምህራን የማንበብ ክሂል ትምህርት የክፍል ውስጥ አተገባበር ምን እንደሚመስል በንጽጽር መፈተሽ ነው፡፡ ይህንም አላማ ከግብ ለማድረስ አጥኚዋ የተጠቀመችው ቅይጥ የምርምር ዘዴን ነው፡፡ ጥናቱ የተካሄደባቸው ትምህርት ቤቶችም ላፍቶ 2ኛ ደረጃና ለቡ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ሲሆኑ፣ የተመረጡትም በአመቺ የናሙና ዘዴ ነው፡፡ በእነዚህ ትምህርት ቤቶች በመደበኛው መርሃ ግብር የሚያስተምሩ አራት እንዱሁም በማታው መርሃ ግብር የሚያስተምሩ አራት በድምሩ ስምንት መምህራንን በጠቅላይ የንሞና ዘዴ በመምረጥ በእያንዳንዱ መምህር ሶስት ሶስት ጊዜ በድምሩ ለሃያ አራት ጊዜ የክፍል ምልከታ በማድረግ በተጨማሪም ለመምህራኑ ቃለመጠይቅ በማቅረብና ተማሪዎችን የጽሐፍ መጠይቅ በማስሞላት ለጥናቱ አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎች ተሰብስበዋል፡፡ እነዚህ መረጃዎችም በገለፃና በቁጥር የመረጃ መተንተኛ ዘዴዎችን በቅንጅት በመጠቀም በንጽጽር ተተንትነው ቀርበዋል፡፡ ከትንተናው የተገኘው ውጤትም የሚያመለክተው መምህራኑ የማንበብ ክሂል ትምህርትን በሚያስተምሩበት ወቅት በአብዛኛው የሚከተለት የጮክታ ንባብ መሆኑ፤ በንባብ ክሂል ትምህርቱ አተገባበር የመደበኛው መርሃ ግብር መምህራን ከማታው መርሃ ግብር መምህራን የተሻለ መሆናቸው፤ እንዱሁም ለማታው መርሃ ግብር የተመደበው ክፍለጊዜ ዝቅተኛ መሆን የማንበብ ክሂል ተግባራቱን በአግባቡ ለመተግበር እንቅፋት መሆኑን የጥናቱ ውጤት ያመለክታል፡፡ የጥናቱን ውጤት መሰረት በማድረግም መምህራን ውጤታማ የሆነ የማንበብ ክሂል ትምህርትን ለማስተማር የሚረደ የማንበብ ክሂል ተግባራትን በአግባቡ ቢተገብሩ፤ በመማሪያ መጻህፍት ውስጥ ካለ ምንባቦች በተጨማሪ የተለያዩ የስነ-ጽሐፍ ውጤቶችን እያቀረቡ ቢያስተምሩ፣ የትምህርትቤቶቹ አስተዳደር ተማሪዎቹም ሆነ መምህራን ሊጠቀሙባቸው የሚገቡ የተለያዩ የስነ-ጽሐፍ ምንጮችን በትምህርት ቤቱ ቤተ-መጻህፍት ውስጥ ተሟልተው እንዲቀርቡ ቢደረግ የሚሉ አስተያየቶች ተጠቁመዋል፡፡
  • Item
    ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት በአራቱ ሃይማኖቶች የአማርኛ መዝሙራት ግጥሞች
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2022-06) የማርያምወርቅ ተሻገር; ዶ/ር የወንድወሰን አውላቸው
    ይህ ጥናት “ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት በአራቱ ሃይማኖቶች የአማርኛ መዝሙራት ግጥሞች ውስጥ” በሚል ርእስ የተሠራ ነው፡፡ እነዚህም ሃይማኖቶች የኢትዮጵያ ኦርቶድክስ ተዋሔድ ቤተ ክርስቲያን፣ የእስልምና፣ የካቶሊክ እና የፕሮቴስታንት ሃይማኖቶች ናቸው፡፡ በእነዚህ መዝሙራት ውስጥ ያለ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነትን የተመለከቱ ጉዳዮች ተተንትነውበት የተሠራ ጥናት ነው፡፡ ጥናቱ ዓላማ አድርጎ የተነሣው ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት በአራቱም ሃይማኖቶች የመዝሙር ግጥሞች እንዴት እንደቀረበ ለመፈተሽ ነው፡፡ ጉዳዩን የተመለከቱ ዝማሬዎችን ሰብስቦ በርእሰ ጉዳዮቻቸው በመባደን ይዞታቸውን እያብራራ አስፍሯል፡፡ ይህ ዓላማ ግቡን እንዲመታ በአራቱም ሃይማኖቶች ውስጥ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን የሚያቀነቅኑ መዝሙራት የትኞች ናቸው? ምን ብለው ነው ያነሡት? ምንስ ፊይዳ ነበራቸው? የሚሉ ጥያቁዎችን በማንሣት ጥናቱ የሚፈልገውን መረጃ እንዲያገኝ አድርጓል፡፡ የጥናቱ ወሰንም ጉደዩን የተመለከቱ መዝሙሮቹ፣ ነሽዳዎች፣ መንዙማዎች ከ1983 ሰኔ እስከ 2013 ነሐሴ የተሠሩትን ያካትታል፡፡ መዝሙሮቹ በተለይ በኢህአዲግና በብልጽግ የአስተዳደር ዘመን የተዜሙ ሲሆኑ በመንፈሳዊ መዝሙር ውስጥ የተለያዩ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነትን በማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ጉዲዮች ውስጥ እንዴት እንደቀረቡ በመተንተን ድምፀታቸውን ያጠና ነው፡፡ በጥናቱ ከርእሰ ጉዲዩ ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ቀዳማይና ካልአይ የመረጃ ምንጮች ተካተውበታል፡፡ በዋናነት የተጠቀመው የመረጃ ምንጭ በሰነድ ምርመራ የተገኙ መረጃዎችን እንደአስፈላጊነቱ ተጠቅሟል፡፡ ለሰበሰብኩት መረጃ መተንተኛ የንድፈ ሐሳብ ማሕቀፍች ብዬ የተጠቀምባቸው ተግባራዊ ወይም ጠቀሜታዊ ሲሆን ሁለተኛው ማኅበራዊ ሂስ ነው፡፡ የመተንተኛ ስሌቱ ዯግሞ የይዘት ትንተና (content analysis) ነው፡፡ የሰበሰብካቸው 1900 መዝሙራት መካከል ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ላይ የሚያጠነጥኑ 49 መዝሙራትን አግኝቻሁ፡፡ ይህም ያነሣሁትን ርእሰ ጉዳይ በቀጥታ ሊያገዝፉልኝ የሚችሉትን ብቻ የተመለከተ ነው፡፡ መዝሙራቱ በአጥኚው ሲቃኙ በመዝሙሮቻቸው የምእመናኑን መሻትና ብሶት፣ ሕዝባቸው እና ሀገራቸው ከፈጣሪያቸው ጋር ያላቸውን የግንኙነት ለሥላሴና ሽክረት በዘመን መንፈስ ውስጥ በልዩ ልዩ ድምፀት ያለ ፍርሃት ገልጸዋል፡፡ መዝሙሮቹ፣ ነሺዲዎቹ፣ መንዙማዎቹ በኢህአዲግ ብልጽግና ሥርዒተ መንግሥት ጊዜ የቀረቡ በመሆናቸው የየዘመኑን ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ክሥተቶችን ምን ነበርነትን እና ምን አለነትን ያሳዩ የዘመኑ የሕዝብ ድምፅ ሆነው በጥናቱ አገልግለዋል፡፡
  • Item
    በወላይታ ዞን በአረካ ከተማ ሙሉ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት በወላይተኛ ቋንቋ አፋቸዉን የፈቱ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች በአማርኛ ቋንቋ ትምህርት የአንብቦ መረዳትና የንባብ ልምድ ችሎታ ፍተሻ
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2022-08) ጳውሎስ ጋምቡራ; ደረጀ ገብሬ
    የዚህ ጥናት ዋና አላማ አድርጎ የተነሳው በወላይተኛ ቋንቋ በወላይተኛ ቋንቋ አፋቸዉን የፈቱ የሆኑ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች በአማርኛ ቋንቋ ትምህርት የአንብቦ መረዲትና የንባብ ልምዴ ችሎታ ላይ ያለውን ሚና መፈተሸ የሚል ነው፡፡ ተሳታፉዎች በደቡብ ክልል በወላይታ ዞን በአረካ ከተማ አስተዲደር አረካ ሙሉ አንደኛ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2015 ዓ.ም ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ የሚገኙ በአጠቃላይ ከእያንዳንዱ ሰክሽን 0.5% በመውሰድ ከ264 ተማሪዎች መካከል በቀላል ወይም በተራ ንሞና አመራረጥ ስልት አማካይነት 132 ተማሪዎችን በተጠኝነት ተመርጠዋል፡፡ ከተሳታፉፊዎች መረጃ የተሰበሰበው በሁለት የተለያዩ የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴዎች ነው፡፡ እነሱም የጽሁፍ ፈተናና የጽሁፍ መጠይቅ ናቸው፡፡ ፈተናዎቹ የአንብቦ መረዳት እና የማንበብ ልምድ ችሎታን ለመለካት ሲያገለግል የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴ በመሆን አገልግሎል፡፡የተሰበሰቡት መረጃዎች አስተማማኝነት ተገቢነትና የውጤት ስርጭት ወጥነት ተሰልቶ ከተረጋገጠ በኋላ ሁሉም መረጃዎች በመጠናዊ ወይም ገላጭ እና ዓይነታዊ ምርምር ዘዴ አማካኝነት ስታትስቲክሶች ተተንትነው ተብራርተዋል፡፡ በመሆኑም የተገኘው መረጃ በስታስቲካሌ ዘዴና በመቶኛ ፐርሰንት በመቀመር መለኪያ /አማራጮች / Likert scale የ“SPSS” ሶፍትዌር መለኪያዎችን በቅንነት የባለሙያ ድጋፍ አማካይነት እንድወጣ ተደርግዋል፡፡ መለኪያዎች /አማራጮች/ Likert scale የመፈተሻ ዘዴዎችን ለመጠቀም የሚያስችል በመሆኑ ተግባራዊ የተደረጉት በመተንተኛ ዘዴዎች ላይ Gray (2004) እና Karl pearson, (1888) ናቸው፡፡ በትንተናው መሰረት በአማርኛ ቋንቋ ትምህርት የአንብቦ መረዲትና የንባብ ልምዴ ችሎታን በመጠኑ መካከለኛ ሆኖ ተገኝቷል፡፡የአማርኛ ትምህርት የአንብቦ መረዳት ችሎታ ፈተና ዉጤት አማካይ 62.18 ሲሆን የተማሪዎች የንባብ ልምድ አማካይ ዉጤት ዳግሞ 65.73 ነዉ፡፡ እንዴሁም የአንብቦ መረዳት ችሎታ ፈተና ዉጤት የተገኘዉ መደበኛ ልይይት/sd/ 0.247487 ስሆን የተማሪዎች የማንበብ ልምዴ ፈተና ዉጤት የተገኘዉ መደበኛ ልይይት/sd/ ዳግሞ 0.908818 ነዉ፡፡ በትንተናው መሰረት የተገኘ ውጤት የበርካታ ተማሪዎች በማኔስ ላይ ሲሆን ዳግሞ ጥቂቶቹ በማደግ ላይ መሆኑን አስቀምጧል፡፡
  • Item
    በኦሮምኛ ቋንቋ አፋቸውን የፈቱ ተማሪዎች የአማርኛ ቃላትን የመማር ብልሃቶች ትንተና (በሩፍሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በአስረኛ ክፍል ተማሪዎች ተተኳሪነት)
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2022-07) ያሲን አደም ጌታነህ; ዳዊት ፍሬህይወት (ዶ/ር)
    የዚህ ጥናት አብይ አላማ በኦሮምኛ ቋንቋ አፋቸውን የፈቱ ተማሪዎች የቃላት መማር ብልሃቶችን መለየትና መተንተን ነበር፡፡ የጥናቱ ተሳታፊዎች በሩፍሴ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2015 ዓ.ም ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ የሚገኙ በአመቺ ንሞና ዘዴ የተመረጡ 70 የአስረኛ ክፍል ተማሪዎች ናቸው፡፡ የጥናቱ የመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያዎችም፡- የጽሁፍ መጠይቅ በዋናነት ሲሆን ቃለመጠይቅ በአጋዥ የመረጃ መሰብሰቢያነት ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡ እነዚህ መረጃዎችም በአይነታዊና መጠናዊ የመረጃ መተንተኛ ተተንትነው ገላጭ በሆነ ስልት ቀርበዋል፡፡ በውጤት ትንተናው መሰረትም በኦሮምኛ ቋንቋ አፋቸውን የፈቱ ተማሪዎች የአማርኛ ቃላትን የሚለማመዱበት ስልት ቃላትን የመማር ብልሃት አጠቃቀማቸው በብቃት ላይ የተመሰረተ ሆኖ አልተገኘም፡፡ ተጠኚ ተማሪዎች በትውስታ ብልሃት ስር ከቀረቡላቸው ስድስት ብልሃቶች አብዛኞቹ 177(252.9%)ያህልጊዜ በመደጋገም አልፎ አልፎ እንደሚጠቀሙ ተረጋግጧል፡፡ አዕምሮታዊ ብልሃቶችን በተመለከተ ለተማሪዎች ከቀረቡላቸው አስራአንድ ጥቅል ብልሃቶች አብዛኞቹን ብልሃቶች 425(607%)ያህል ጊዜ ብልሃቱን በመደጋገም አልፎ አልፎ ተጠቅመዋል፡፡ በአንጻሩ ደግሞ አካካሽ ብልሃቶችን በተመለከተ 101(144.3%)ያህል ጊዜ ደጋግመው ሁልጊዜ እንደተጠቀሙ ሲገልጹ፣ ልዕለአዕምሮታዊ ብልሃቶችን ደግሞ 122(174.2%) ያህልጊዜ ደጋግመው አልፎአልፎ እንደሚጠቀሙ መረጃው ያመለክታል፡፡ በተመሳሳይ መልኩም በስሜትነክ ቁጥጥር ብልሃቶች ስር ከቀረቡላቸው ሶስት ብልሃቶች አብዛኞቹ ተማሪዎች144(205.5%) ጊዜ በመደጋገም አልፎ አልፎ ሲጠቀሙ፣ማህበራዊ ብልሃቶችን በተመለከቱ ደግሞ 61(87.1%) ያህል ጊዜ አልፎ አልፎ በመደጋገም እንደሚጠቀሙባቸው የትንተናው ውጤት ያሳያል፡፡ በመሆኑም ተጠኚ ተማሪዎች በተደጋጋሚ አብዝተው የሚጠቀሙት አካካሽ ብልሃቶችን ሲሆን ሌሎቹን ብልሃቶች ግን ሁልጊዜ በመደጋገም አብዝተው እንደማይጠቀሙባቸው ውጤቱ ያሣያል፡፡ እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ የአማርኛ ቋንቋ መምህራን ተማሪዎች በራሳቸው ጥረት እንዲለማመዱ መንገድ ቢያመቻቹላቸውና ክትትል ቢያደርጉ፣ እንዲሁም የአማርኛ መማርያ መጽሐፍ አዘጋጆች የቃላት መማር ብልሃትን እንደ አንድ የቃላት ትምህርት ማቅረቢያ መንገድ ቢጠቀሙበት የሚልየመፍትሄ ሀሳቦች ተጠቁመዋል፡፡
  • Item
    የሰዋስው ትምህርት ይዘቶች አቀራረብና አደረጃጀት ግምገማ (ለኢ-አፈ ፈት ተማሪዎች በተዘጋጁት የ7ኛና 8ኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መጻህፍት ተተኳሪነት)
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2023-10) ወይንሸት አሰፋ; ጌታሁን አማረ(ፕ/ር)
    የዚህ ጥናት ዋና ትኩረት በኦሮሚያ ክልል በ2014ዓ.ም ኢ-አፈ ፈት ለሆኑ የ7ኛና የ8ኛ ክፍል አማርኛ ቋንቋ መማሪያ መጻህፍት ውስጥ የተካተቱት የሰዋስው ትምህርት ይዘቶች አቀራረብና አደረጃጀት የሚፈትሽ ነው፡፡ ጥናቱ ጥያቄ አድረጎ በተነሳባቸው ነጥቦች ዙሪያ የቋንቋ ምሁራን ያቀርቧቸውን ንድፈ ሀሳባዊ መሠረቶች መንደርደሪያ በማድረግ በሰዋስው ትምህርት ይዘቶች አቀራረብና አደረጃጀት መርሃ ስር መነሳት ያለባቸውን ነጥቦች ለመመለከት ሞክሯል፡፡ የጥናቱ ዓብይ የመረጃ ምንጭ የሰነድ ፍተሻ ሆኖ ከተማሪዎችበፅሁፍ መጠይቅና ከመምህራን በቃለ መጠይቅ በተገኙ ምላሾችምመረጃውን ለማጠናከር ተሞክሯል ፡፡ ከዚህ የመረጃ ምንጮች የተገኙ ምላሾችም ባላቸው ተዛማጅነት አንድ ላይ እየተደራጁ በምዕራፍ አራት ስር ተተንትነዋል፡፡ ከጥናቱ የተገኘው ውጤት እንደሚያመለክተው ከይዘቶች አቀራረብ አንጻር የ7ኛና የ8ኛክፍል ውጤት ተኮር አቀራረብን ሰፊ ሽፋን የሰጠ ሲሆን የ7ኛና የ8ኛ ክፍል መማሪያ መፃህፍት ከዝርዝር ወደ አጠቃላይ አቀራረብ ላይ የበለጠ ትኩረት በመስጠት አብላጫውን ሽፋን እንዲይዙ በማድረግ የቀረቡ ናቸው፡፡ከተገቢነት አንፃርም በአብዛኛው መፃህፍቱ ለተዘጋጁላቸው ተማሪዎች ዳራዊ እውቀት፣የመስራት አቅም፣የመረዳት ችሎታ ተገቢ ያልሆኑ ቸግሮች እንዳሉባቸው ለማስተዋል ተችለዋል፡፡ከአደረጃጀት አንፃርም በ7ኛና 8ኛ ክፍል መማሪያ መፃህፍት ውስጥ የተካተቱ የሰዋስው ትምህርት ይዘቶች አብዛኞቹ ተደጋግመው የቀረቡ እንዳልሆኑና ጥልቀታቸውም እየጨመረ የመሄድ ችግር ያለባቸው እንዳሉ ተስተውሏል፡፡ በሁለቱም መማሪያ መፃህፍት መካከል ተለጣጣቂነት የሚታይባቸው ይዘቶችም እንዳሉ ሁሉ የተወሰኑት ስፋትናጥልቀታቸው እየጨመረ የማይሄዱ ይዘቶች እንዳሉ ለማየት ተችሏል፡፡
  • Item
    አማርኛን እንደ ሁለተኛ ቋንቋ የሚማሩ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች በ8ኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መጽሐፍ ውስጥ የቀረቡ የማዳመጥ ክሂል ትምህርት ክንውኖች የክፍል ውስጥ አተገባበር ግምገማ ፤በአርሲ ዞን ዶዶታ ወረዳ አርጊቲ ደነባ አንደኛ ደረጃ 2ኛ እርከን ትምህርት ቤት
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2023-09) አየለች ጩቃላ; ግርማ ገብሬ (ዶ/ር)
    ይህ ጥናት በዋናነት አላማ ያደረገዉ አማርኛን እንደ ሁለተኛ ቋንቋ የሚማሩ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች የማዳመጥ ክሂል ትምህርት የክፍል ዉስጥ አተገባበር ግምግማ ላይ ሲሆን ተጠኚዎቹ በአመችነት የናሙና አመራረጥ የተመረጡና ገላጭ የትንተና ዘዴን የተከተለ ጥናት ነዉ፡፡ ጥናቱም የተከናወነው በአርሲ ዞን ዶዶታ ወረዳ አርጊቲ ደነባ አንደኛ ደረጃ የመንግስት ትምህርት ቤት በ2015 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች በአማርኛ ቋንቋ ኢ-አፍፈት የሆኑ 75 በተመረጡ ተጠኚ ተማሪዎች ላይ ነዉ፡፡ አጥኚዋ ለጥናቱ አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎችን በጽሁፍ መጠይቅ፣ በቃል መጠይቅና የክፍል ዉስጥ ምልከታ በማድረግ ሰብስባለች፡፡ በጽሁፍ መጠይቅና በቃለ መጠይቅ እንዲሁም በምልከታ በተገኘዉ ምላሽ በቅድመ ማዳመጥ ፣በማዳመጥ ጊዜ እና በድህረ ማዳመጥ ጊዜ ክፍል ዉስጥ አተገባበር ምን እንደሚመስል የመጠይቆቹን ጥያቄዎች በሰንጠረዥ ዉስጥ በቁጥርና በመቶኛ እንዲሁም በገለጻ ተተንትኗል፡፡ በመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያዎች አማካይነት በተገኙ የመረጃዎች ትንተና ዉጤት መሰረት ተጠኚ ተማሪዎች የማዳመጥ ክሂል ትምህርት በክፍል ዉስጥ ሲተገበር የተገኘው ምላሽ እንደማይተገበርና ቢተገበርም አተገባበሩም ደካማ መሆኑ ከጥናቱ የተገኘዉ ዉጤት ያሳያል፡፡ ከተጠኚ መምህራን የተገኘ ምላሽም የማዳመጥ ክሂል ይዘቶችን በክፍል ዉስጥ የሚተገብሩት አልፎ አልፎ እንደሆነ በጥናቱ ዉጤት ታዉቋል፡፡ ሌላዉ መምህራን ከተማሪዎቹ ችሎታ፣ ዳራና ፍላጎት ጋር የሚጣጣሙ ይዘቶችን በማዘጋጀት እንደማያቀርቡ በጥናቱ ዉጤት ዉስጥ ለማወቅ ተችሏል፡፡ እንዲሁም ተጠኚዎቹ ክሂሉን ለማዳበር ይችሉ ዘንድመምህራን ክሂሉን ሲተገብሩ የተለያዩ ስልቶችን ለምሳሌ የተቀረጹ ድምጾችን፣ አጫጭር ታሪኮችንና ሥነጽሁፋዊ ስራዎችን ወደ ክፍል ዉስጥ በማምጣት እንደማያስደምጧቸዉና በዚህም ምክንያት ዉጤታማነቱ ዝቅተኛ መሆኑን አጥኚዋ ተገንዝባለች፡፡ ከዚም በተጨማሪ የማዳመጥ ክሂል ትምህርት አተገባበር ላይ ትልቅ ተግዳሮት የሆነና ተጠኚ መምህራንም የገለጹት ጉዳይ፡- ተጠኚዎቹም ሆኑ ተማሪዎች ቋንቋዉን የሚማሩት እንደ ሁለተኛ ቋንቋ ስለሆነ ተጠኚዎቹ ከወዲሁ የቋንቋዉ ትምህርት ይከብዳል፣ አይገባኝም በማለት እና ለቋንቋዉ ትምህርት ያላቸዉ ፍላጎት አናሳበመሆኑ ከየት መጣ የክሂሉን እዉቀት በታሰበዉ ልክ መተግበር አለመቻላቸዉን በጥናቱ ዉስጥ ተጠቅሷል፡፡ ሌላዉ ጉዳይ ለቋንቋዉ መምህራን ለክሂሉ መዳበርም ሆነ ለቋንቋዉ ትምህርት ዉጤታማነት አጫጭር ስልጠናና ዎርክ ሾፖች ስለማይሰጣቸዉ በክሂሉ አተገባባር ላይ ተጽእኖ እነዳሳደረባቸዉ በጥናቱ ዉስጥ ተረጋግጧል፡፡
  • Item
    የአማርኛ ሰዋስው ትምህርት የክፍል ውስጥ አተገባበር ፍተሻ (በሰሜን ሸዋ ዞን በደብረሊባኖስ ወረዳ በድሬ ጅቦ እና በአባገዳ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣በ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ተተኳሪነት የቀረበ ጥናት)
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2023-09) በጽጌ ግርማ; ዳዊት ፍሬሕይወት (ዶ/ር)
    የጥናቱ አብይ ዓላማ የመምህራንን የሰዋስው ትምህርት የክፍል ውስጥ አተገባበር በመፈተሽ የተስተዋሉ ችግሮችን ለይቶ በመጠቆም የመፍትሄ አቅጣጫዎች ተጠቁመዋል፡፡ ጥናቱ አይነታዊ የምርምር ዘዴን ተግባራዊ አድርጓል፡፡ የጥናቱ ተሳታፊ ተማሪዎች ሁለተኛ ቋንቋቸው የሆኑ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች እና የ8ኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መምህራን ሲሆኑ እነዚህ ዋነኛ የመረጃ ምንጮች ናቸው፡፡ ጥናቱ ጥያቄ አድርጎ በተነሳባቸው ነጥቦች ዙሪያ የቋንቋ ምሁራን ያቀረቧቸውን ንድፈሃሳባዊ ብያኔዎች መሰረት በማድረግ የሰዋስው ትምህርት አተገባበር በሚለው ርዕስ ስር መነሳት ያለባቸውን ነጥቦች በዝርዝር ለማየት ሞክሯል፡፡ የጥናቱ አብይ የመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያ የክፍል ውስጥ ምልከታ ሲሆን ከተማሪዎች የጽሑፍመጠይቅ እና ከመምህራን በቃለመጠይቅ የተገኙ መረጃዎችም በመጠናዊና በአይነታዊ የመረጃ መተንተኛ ስልቶች አንድ በአንድ ለመተንተን ተሞክሯል፡፡ ከመረጃ ምንጮቹ የተገኙት መረጃዎችም እርስ በእርስ ባላቸው ተዛምዶ አንድ ላይ በማደራጀት በምዕራፍ አራት ስር ለመተንተን ተችሏል፡፡ ከጥናቱ የተገኘው ውጤት እንደሚያመለክተው ታላሚዎቹ መምህራን በክፍል ውስጥ በትግበራ ወቅት የሰዋስው ትምህርት ይዘትን ሲያቀርቡ የተለያዩ የማስተማሪያ ስልቶችን አለመጠቀማቸው፣ ተማሪዎች በቡድን እንዲወያዩ እና ሀሳባቸውን በነጻነት እንዲያንጸባርቁ እድል አለመስጠት፣ የሰዋስው ትምህርት አቀራረብ ደረጃዎችን አለመጠቀም፣ እንዲሁም ምጋቤ ምላሽ አሰጣጥ ላይ ድክመት እንዳላቸው መመልከት ተችሏል፡፡በሌላ በኩል ታላሚዎቹ መምህራን ከተማሪዎቻቸው ጋር ጥሩ መስተጋብር እንዳላቸው ታይቷል፡፡በአጠቃላይ የታዩትን ጠንካራ ጎኖች በማበረታታት፣ ደካማ ጎኖቹ ደግሞ ሊቀረፉ የሚችሉበትን እና የመማር ማስተማሩን ሂደት የተሻለና ውጤታማ ያደርጋሉ ተብለው ከታመነባቸው ሀሳቦች ውስጥ የመምህራንን የትምህርት ዝግጅት በተመለከተ መምህራኑ ትምህርቱን ከማቅረባቸው በፊት በቂ ዝግጅት ቢያደርጉ፣ የሰዋስው ትምህርቱን ሲያቀርቡ የማለማመጃ ስልቶችን እንደ ምልልስ፣ሚና ጨዋታ፣የመሳሰሉትን እና የአቀራረብ ደረጃዎችን በክፍል ውስጥ በመጠቀም ቢያስተምሩ፣ሰዋስውን በተናጠል ከማስተማር ይልቅ ከቋንቋ ክሂሎች ጋር አቀናጅተው ቢያቀርቡ፣ ወዘተ. የሚሉትን የመፍትሄ ሀሳቦች በመጠቆም ጥናቱ ተጠናቋል፡፡
  • Item
    ደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ት/ቢሮ በተዘጋጀው የ8ኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መጽሐፍ ውስጥ የተካተቱ የአፍልቆት ክሂሎችን ለማዳበር የቀረቡ መልመጃዎች አቀራረብና አደረጃጀት ትንተና
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2023-09) ተሰማ ተስፋዬ; ግርማ ገብሬ (ዶር)
    የዚህ ጥናት ዓላማ በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ አማርኛ እንደ ሁለተኛ ቋንቋ በሚል ርዕስ ለስምንተኛ ክፍል አዲስ በተዘጋጀው የአማርኛ መማሪያ መጽሀፍ ውስጥ የቀረቡትን የአፍልቆት ክህሎችን ለማዳበር የቀረቡ መልመጃዎች አቀራረብና አደረጃጀት በመፈተሽ፣ የታዩ ጠንካራ ጎኖች ይበልጥ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ፣ ድክመቶችም መጽሀፉ ሲሻሻል ትኩረት አግኝተው የሚሻሻሉበትን ሀሳብ ለመስጠትና አሁን በማስተማር ላይ ሆነው ይህን ጥናት ሊያገኙ የሚችሉ የክፍሉ መምህራን ሲያስተምሩ የታዩ ክፍተቶችን በራሳቸው ሊሞሉ የሚያስችላቸውን የማሻሻያ ሀሳብ ለመስጠት ነው፡፡ የጥናቱ ዓላማ ከግብ ይደርስ ዘንድ የመረጃ ምንጮቹን የሰነድ ፍተሻና ለክፍሉ መምህራን የሚቀርብ የጽሁፍ መጠይቅ አድርጓል፡፡ በሰነድነት የሚፈተሸውም የስምንተኛ ክፍል አማርኛ ቋንቋ መማሪያ መጽሀፍ ነው፡፡ ለጽሁፍ መጠይቅ የመረጃ ምንጭ የሆኑ መምህራን በከምባታ ጠምባሮ ዞን፣በዱራሜ ከተማ አስተዳደር ስር ባሉት አራት የመጀመሪያ ደረጃ የመንግስት ትምህርት ቤቶች ውስጥ አማርኛ ቋንቋ ከሚያስተምሩት መምህራን መካከል ተመርጠው የቀረቡ ናቸው፡፡ ከሁለቱም የመረጃ ምንጮች የተሰበሰቡ መረጃዎች በአይነታዊና በመጠናዊ ዘዴዎች በመተንተን በማብራሪያዎች ተደግፈው ቀርበዋል፡፡ ትንታኔው የሚያሳየው ለአፍልቆት ክሂሎች ማዳበሪያነት የቀረቡት መልመጃዎች ከይዘት ምርጫ አንጻር ወቅታዊነት፣ ተገቢነትና ተተግባሪነት ያላቸው ይዘቶች እንደሆኑ ጥናቱ አረጋግጧል፡፡ ጥናቱ ከአደረጃጀትም አንጻር ተከታታይነቱ በጥንካሬ የተገመገመ ነው፡፡ የመናገር ክሂል በይዘት የታጨቀ ነው፡፡ ከክፍል ትምህርቱ ይዘት 33.3% የሚሆነውን የተሸፈነው በንግግር ነው፡፡ ስለዚህ ዝግጅቱ የአደረጃጀት ችግር እንዳለበት ለንግግር ክሂል የተሰጠው ሰፊ ሽፋን ማሳያ ነው፡፡ በተቻለ ፍጥነት መሻሻል ካለባቸው ችግሮች ዋነኛው የንግግርን ሽፋን ማስተካከል ነው፡፡ በተጨማሪም ጥናቱ የመጽሀፉ ዝግጅት የተለጣጣቂነት ችግር እንዳለበት ያሳያል፡፡ ይዘቱ ከቀላል ወደ ውስብስብና ከባድ ስፋትና ጥልቀት እየጨመረ መሄድ ሲገባው ከአደረጃጀትም ሆነ ከአቀራረብ አንጻር ወጥነት የጎደለው አካሄድ ተከትሏል፡፡ ይህም ክፍተት በሚመለከተው አካል ሊስተካከል ይገባል የሚል አመለካከት ያላቸው የመፍተሄ ሀሳቦች ቀርበዋል፡፡