Amharic Language, Literature and Folklore

Permanent URI for this collection

Browse

Recent Submissions

Now showing 1 - 20 of 456
  • Item
    አንብቦ መረዳት እና የመጻፍ ክሂል ቅንጅታዊ የይዘት አቀራረብ ትንተና በ8ኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሐፍ ተተኳሪነት (በ2015 ዓ.ም በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ የታተመ)
    (አዲስ አባባ ዩኒቨርሲት, 2023-08) ሰይድ አሊ ይመር; አቶ ደረጀ ገብሬ
    ይህ ጥናታዊ ፅሑፍ ዋና ዓላማው በ2015 ዓ/ም ታትሞ በስራ ላይ የዋለው የ8ኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ ማስተማሪያ መፅሀፍ ውስጥ የአንብቦ መረዳትና የመፃፍ ክሂሎች ቅንጅታዊ የይዘት አቀራረብ መፈተሽ በ8ኛ ፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍ ተተኳሪ ነው፡፡ ይህን ዓላማ ለማሳካትም በሰነድ ፍተሻ እና በቃለመጠይቅ መረጃዎች ተሰብስበዋል፡፡ የጥናቱ ዓላማ በተማሪው መማሪያ መፅሀፍ ውስጥ የመፃፍ ክሂልና የአንብቦ መረዳት ክሂልን አዋህዶ ይዘቶችንና መልመጃዎችን መቅረባቸውና አለመቅረባቸው መመርመር ፤የአንብቦ መረዳት እና የመፃፍ ክሂል አቀናጅቶ ለማስተማር የቀረቡ ምንባቦች የቋንቋ ግልፅነት ማየትና ሁለቱን ክሂሎች አቀናጅቶ ለማስተማር የቀረቡትን መልመጃዎች ግልፅነት መመርመር ነው፡፡ ይህንን ጥናታዊ ፅሁፍ ከፍፃሜ ለማድረስ አጥኝው የተጠቀመ የመረጃ መተንተኛ ዘዴዎች መጠናዊ የምርምር ዘዴ እና ዓይነታዊ የምርምር ዘዴዎች ናቸው፡፡ የመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያዎች ሰነድ ፍተሻ እና ቃለ መጠይቅ ናቸው። ከመረጃዎቹ የተገኙት ውጤቶች የሚያመለክቱት አንብቦ የመረዳትና የመጻፍ ክሂልን የሚመለከቱ ይዘቶች አቀራረብ ለመማር ማስተማሩ ሂደትም ሆነ ለተማሪዎቹ ልምምድ አመቺ መሆናቸውን፤ አንብቦ የመረዳትና የመጻፍ ክሂልን የሚመለከቱ ይዘቶችና መልመጃዎች አቀራረብ የተማሪዎችን ደረጃ፣ዕድሜና ችሎታ እንዲሁም ዳራዊ እውቀታቸውን ከግንዛቤ ውስጥ ያስገቡ መሆናቸውን፤የመማሪያ መጽሀፉ አቀራረብ አንብቦ የመረዳትና የመጻፍ ክሂሎች በተቀናጀ መልኩ እንደተዘጋጁና የማስተማሪያ መሳሪያዎቹ አንብቦ የመረዳትንና የመጻፍ ክሂሎችን አቀናጅቶ ለማስተማር እገዛ እንዳላቸው ጥናቱ ፍተሻ አድርጓል፡፡ በዚህ ጥናታዊ ፅሁፍ መጨረሻ ውጤት የሚያሳየው የአንብቦ መረዳት እና ለፅህፈት ክሂል አቀናጅቶ ለማስተማር የቀረቡት ምንባቦች ቋንቋውን እንደሚረዱት ሆኖ ቀርቧል፡፡ቢሆንም የተወሰኑ ይዘቶች እና መልመጃዎች የቋንቋ ግልፅነት የሌላቸው መሆኑን ጥናቱ ያሳያል፡፡ በመጨረሻም ይህ ጥናታዊ ፅሁፍ የሚሰጠው ማሻሻያ ሃሳብ ፤ተማሪዎች አንብበው የተረዱትን ሀሳብ በፅሁፍ ለመግለፅ ይዘቶች እና መልመጃዎች በሰፊው ቢዘጋጅ እና ተቀናጅተው ቢቀርቡ፡፡ የአንብቦ መረዳት እና የፅህፈት ክሂልን በቅንጅት ለማስተማር የቀረቡት ምንባቦች የሃሳብ ግልፅነት የሌላቸው መሆኑን ሲያሳይ ፤ምንባቦች ተሻሽላው ቢቀርቡ በማለት ጥናታዊ ፅሁፍ የመፍትሔ ሀሳብ አቅርቧል፡፡
  • Item
    በ2012 ዓ.ም በፋና“ጉዞ ኢትዮጵያ”ና በኢቢኤስ “ኢትዮጵያን እንወቅ” ሳምንታዊ የቴሌቭዥን ፕሮግራሞች ውስጥ የተካተቱ ፎክሎራዊ ጉዳዮች ትንተና
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2024-08) ሸዋቀና ታህለው; ዓለሙ ካሣዬ (ዶ/ር)
    ይህ ጥናት “በ2012 ዓ.ም በፋና“ጉዞ ኢትዮጵያ”ና በኢቢኤስ “ኢትዮጵያን እንወቅ” ሳምንታዊ የቴሌቭዥን ፕሮግራሞች ውስጥ የተካተቱ ፎክሎራዊ ጉዳዮች ትንተና” በሚል ርዕስ የቀረበ ነው፡፡ በዚህ ጥናት ተተኳሪ በሆኑት ሁለቱ የቴሌቨዥን ተቋማት ሳምንታዊ ፕሮግራሞች ውስጥ የትኞቹ የፎክሎር ዘውጎች ተካተዋል?፤ ፎክሎራዊ ዘውጎቹ ለቴሌቭዥን ጣቢያዎቹ ምን ፋይዳ አላቸው?፤ ለጥናቱ በተለዩት ጣቢያዎች የፎክሎር መካተት ለመስኩ የምርምር ዘርፍ የሚኖረው ፋይዳ ምንድን ነው?። ለሚሉት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ተችሏል፡፡ጥናቱ የተከተለው አይነታዊ የአጠናን ዘዴን ሲሆን፤በሰነድ ፍተሻና በቪዲዮ ምልከታ የተሰበሰበው መረጃ በገለጻና በትረካ ስልት ትንተና ተደርጎበታል፡፡በመጨረሻም አራቱ የፎክሎር ዘውጎች ሥነ-ቃል፣ ሀገረሰባዊ ልማድ፣ ሀገረሰባዊ ትውን ጥበብና ቁሳዊ ባህል በተተኳዋሪ የቴሌቭዥን ጣቢያዎች መካተታቸው በጥናቱ ተረጋግጧል፡፡ ፎክሎሮቹ የሚያስገኟቸውን ፋይዳዎች በተመለከተም ማሕበረሰብን ከማስተማር፣ከቱሪዝም፣ከቴሌቭዥን ፕሮግራም፣ከጥናትና ምርምር፣ከመቀስቀስና ከማንቃት አኳያ አይተኬ ሚና ያላቸው መሆኑ ተመላክቷል፡፡ እንዲሁም የትረካ ስልትን የማሳመር፣የፕሮግራም ተደማጭነትን የማሳደግ ሚና ያላቸው መሆኑ፤ ለማስታወቂያ ስራዎች ተደራሽነትና አይረሴነት የሚጫወቱት ሚና መኖሩ፣ የታሪክ ጭብጥን ለማጉላትና ገጸ-ባህርያትን ለማቅረብም የማይናቅ ድርሻ ያላቸው መሆኑ፣ አድማጭና ተመልካቾች ለጣቢያዎቹ አድማጮችና ተመልካች ደንበኞች ሆነው እንዲቀጥሉ የማድረግ ሚና እንዳላቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡በመጨረሻም አጥኚው ፎክሎር ለማኅበረሰብ የሚያሰገኛቸው ጠቀሜታዎች ዘላቂነት ይኖራቸው ዘንድ በዚህ ጥናት ተተኳሪ የሆኑትን ጨምሮ በተለያዩ ሚዲያዎች የተሰማሩ የፕሮግራም አቅራቢ ጋዜጠኞች ፎክሎሮችን በመዘገብና ሰንዶ በማቅረብ ተግባር በመትጋት ቁሳዊም ሆነ መንፈሳዊ ማህበረሰባዊ እሴቶችን ለትውልድ ለማሻገር ቢሞክሩ በሚል የመፍትሄ ሐሳቡን ለመጠቆም ሞክሯል፡፡
  • Item
    የሴቶች ተሞክሮ በተመረጡ የአማርኛ ግለታሪኮች
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርሰቲ, 2024-08) ብሌን መንግስቱ; የወንድወሰን አውላቸው(ዶ/ር)
    የዚህ ጥናት ዋና ዓላማ በተመረጡ የሴቶች ተሞክሮ በአማርኛ ግለ ታሪክ ፍተሻ ነው፡፡ ጥናቱ ንድፍ አይነታዊ ገላጭ የጥናት ንድፍ የተከተለ ነው፡፡ የመረጃ ምንጮች ሁለተኛ ደረጃ (ዳህራይ) የመረጃ ምንጭ ነው፡፡ ይህም ማለት በግለሰቦች በግላቸው የተፃፉ የአማረኛ ግለ ታሪኮች ትሙት ግድ የለም በዶ/ር ትግስት ግርማ ፣የፀሐይ ጉዞ ወ/ሮ ፀሐይ ይትባረክ የውብ የውብ ድንበር እውተኛ ታሪክ በወ/ሮ ውብ ድንበር ነጋሽ የተፃፈ የአማረኛ ግለ ታሪክ መጽሀፍት መሰረት አድርጎ የተሰራ ጥናት ነው፡፡ የናሙና አመራረጥ አላማ ተኮር ነው፡፡ የተመረጡ የአማረኛ ግለ ታሪክ መፅሀፍት በዓላማ በራሱ አነሳሽነት በቀላሉ በገበያ ላይ የሚገኙ የቅርብ የታተሙ መጽሀፍት በመሆኑ ጭምር ነው፡፡ የመረጃው ትንተና ዘዴ ይዘት ትንተና ላይ አተኩሯል፡፡ ማለትም በመጽሀፍ ውስጥ የተካተቱ በተለዩት ርእሰ ጉዳዮች አንፃር ተተንትኗል፡፡ በዚህ ባሻገር ግለ ታሪኮች በእንስታዊ (ሴትነት ግዴ ትግል) አንፃር በአምስት ቁልፍ ርእሰ ጉዳዮች ማለትም ፓትሪያሊክ(አባዊ) ሥርአት ኢንተርሴክሽናሊቲ ፣የሥርአት ፆታ አፈጻፀም፣ ማህበራዊ ግንባታና የወንድ ዕይታ በሚሉ ርእሰ ጉዳዮች አንፃር ፍተሸ ተደርጋል፡፡ በመሆኑም ግለ ታሪክ አፃፃፍ ላይ የሚመለከተው ክፍል ትኩረት ቢያደርግ የሕይወት ተሞክሮ ማህራዊ ግንኙነት እና የፆታ እኩልነት እዲሁም ጥበብና ትምህርትን በማስፋት ከጾታ ጋር ተያያዞ የሚፈጠሩ ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ፣ፖለቲካዊ ችግሮች ላይ መፍትሔ ለማበጀት ይረዳል፡፡ ቁልፍ ቃላት ፡- የሴቶች ተሞክሮ፣ ግለ ታሪክ አማርኛ እንስታዊ ጽንሰ ሀሳብ፡፡
  • Item
    የሴቶችና የወንዶች አለባበስና አጊያጊያጥ በመርሐቤቴ ወረዳ
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2024-09) ፍስሃ ጌታቸው; የኔዓለም አረዶ(ዶ/ር)
    ይህ ጥናት በመርሐቤቴ ወረዳ የሴቶችና የወንድች አለባበስና አጊያጊያጥ ላይ የሚያተኩር ነው፡፡ አልባሳትና ጌጣጌጦች በማጥናት የተጠኚውን ማህበረሰብ ፈጠራ ውጤት፣ እምነት፣ መለያና የአኗኗር ዘይቤን መመርመር የመጀመሪያው አነሳሽ ምክንያት ሲሆን በቁሶቹ ላይ የሚስተዋለውን የለውጥ ምክንያት መፈተሸና ቁሶቹን ለቀጣይ ትውልድ በመረጃነት ሰንድ ማቆየት ደግሞ ሁለተኛው የጥናቱ መነሻ ምክንያት ነው፡፡ የዚህ ጥናት ዓብይ ዓላማ ለጥናት በተመረጠው አካባቢ የሚከወኑ የሴቶችና ወንድች አለባበስና አጊያጊያጥ ፋይዳን መመርመር ነው፡፡ እንዲሁም የቁሶቹን አካላዊ ገፅታ ማሳየት፣ ትዕምርታዊ ትርጉም መግለፅ፣ ለውጥ የተስተዋለባቸውንም ሆነ ያልተስተዋለባቸውን ቁሶቹ መመርመር እና ቁሶቹን ለመጪው ትውልድ እንዲሸጋገሩ ሰንድ ማቆየት የሚሉ ንዐሳን ዓላማዎች አሉት፡፡ ጥናቱ ከዓይነታዊ የምርምር ዘዴአንደ የሆነው ገላጭ የምርምር ስሌትን የተከተለ ሲሆን ቀዳማይና ካልዓይ የመረጃ ምንጮችን በመጠቀምና ለጥናቱ አስፈላጊ መረጃዎችን በምልከታ፣ በቃለ መጠይቅና በተተኳሪ የቡድን ውይይት መረጃዎቹ ተሰብስበዋል፡፡ እንዲሁም ዘጠኙ (9) የSchlereth መተንተኛ ሞዴሎች ለመረጃ መተንተኛነት፣መዋቅራዊ ተግባራዊነት እና ለውጥና ቀጣይነት ንድፈ ሃሳቦች ዳግሞ ለጥናቱ መቀንበቢያነት ውለዋል፡፡ በታላሚ ናሙና (Purposive sampling) አመራረጥ ዘዴ መሰረት በወረዳው ከሚገኙ 23 ቀበሌዎች ቁሶቹ እስካሁን ድረስ ሳይበረዙ ያቆዩና ባላቸው የአየር ንብረት ልዩነት መሰረት አምስት ቀበሌዎች፣ እንዲሁም ከወጣት እስከ አዛውንት ያለና ባህሉን በደንብ የሚያውቁ 23 ወንዶችና 13 ሴቶች በድምሩ 36 መረጃ አቀባዮች በሀገር ሽማግሌዎችና በባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት መረጃ ሰጭነት ተመርጠዋል፡፡ በተመረጡ 22 አልባሳት እና 24 ጌጣጌጦች እንዲሁም 9 የፀጉር አሰራር ዓይነቶች ላይ ትንተና ተደርጓል፡፡ ጥናቱ በማህበረሰቡ የሚታወቁ አልባሳትና ጌጣጌጥ የትኞቹ ናቸው? የአለባበስ ሥርዓታቸው ምን ይመስላል? የመልበሻ አጋጣሚዎች የትኞቹ ናቸው? ቁሶቹ በማን መቼ እንዴትና ለምን ይሰራሉ? በየዕዴሜ ደረጃቸው ያለ አልባሳትና ጌጣጌጦች መለያቸው ምንድነው? በአልባሳቱና ጌጣጌጡ ላይ ለሚታዩ ለውጦች ምክንያታቸው ምንድነው? የሚሉ ጥያቄዎችን መልሷል፡፡ ከዚህ አንፃር የሚከተለትን ነጥቦች በጥናቱ ግኝት የተመላከቱ ናቸው፡፡ እነሱም የማህበረሰቡ አልባሳትና ጌጣጌጦች በአካባቢው ከሚገኙ ጥሬ ዕቃዎችና የፊብሪካ ምርት ከሆኑ ግብዓቶች በአካባቢው ሸማኔ፣ ልብስ ሰፉዎች፣ በእደ ጥበብ ሙያተኞች የሚጋጁና ገበያው በሚያቀርባቸው መሰረት የሚገኙ ናቸው፡፡ ከአገልግሎት አኳያ የለባሹን ደህንነት የማስጠበቅ፣ ውበትን የማጉላት፣ ፆታን፣ ማንነትን፣ ዕድሜን፣ ጀግንነትን ኃይማኖትን፣ ማህበራዊ ግንኙነትን፣ ማህበራዊ ደረጃዎችን የሚገልፁ ሲሆን ከመዋቅር አኳያ ደግሞ ቁሶቹ ሰርዓተ ማህበሩ እንዲቀጥል የሚያደርጉ ናቸው፡፡ የቁሶቹ ተምሳሌታዊ ትርጉም የማህበረሰቡን አመለካከት፣ ፍልስፍና፣ እውቀት፣ እምነት፣ ማንነት፣ ማህበራዊ ደረጃ፣ ውበት፣ ፆታ ወዘተ ጉዳዮችን የሚገልፁ ሲሆኑ አሰራራቸው ደግሞ ጥበባዊ፣ ታሪካዊ፣ አካባቢያዊ፣ መዋቅራዊ፣ ማህበረሰባዊ ወዘተ መለያ ያላቸው ናቸው፡፡ እንዲሁም ከለውጥና ቀጣይነት አኳያ ምንም ያልተለወጡ፣ በከፉል የተለወጡ፣ ሙሉ ለሙሉ የተለወጡ ቁሶች መኖራቸው የጥናቱ ግኝት ያመላክታል፡፡ በዚህም መነሻነት የማህበረሰቡ ማንነት መገለጫ የሆኑትን ቁሶች የማልማትና ጠቃሚነታቸውን የማጉላት ስራ በድግግሞሽ ቢሰራ ማህበረሰቡን ለማስተዋወቅ፣ ማንነቱን በዘላቂነት ይዞ ለማስቀጠልና ከባህሉ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚ የሚያደርገው ይሆናል የሚል የይሁንታ ሃሳብ በማቅረብ ጥናቱ ተጠናቋል፡፡
  • Item
    ፕሮጀክት ተኮር መማር፣ በመጻፍ ችሎታና ተነሳሽነት ላይ ያለው ተፅዕኖ፤ በ10ኛ ክፍል አማርኛ ቋንቋ አፍፈት ተማሪዎች ተተኳሪነት
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2024-09) ስመኝ አለምነህ; ጌታሁን አማረ (ፕ/ር)
    የዚህ ጥናት ዓላማ ፕሮጀክት ተኮር መማር፣ ለተማሪዎች የመጻፍ ችሎታ እና ተነሳሽነትመሻሻል ያለውን ሚና መፈተሽ ነው፡፡ ዓላማውን ከግብ ለማድረስም ቅድመ ትምህርትናድኅረ ትምህርት ፈተና ባለቁጥጥር ቡድን ከፊል ሙከራዊ (quasi-expermental) ስልትተግባራዊ ሆኗል፡፡ በጥናቱ የትግበራ ሂደትም አማራ ክልል በአላማ ተኮር ንሞናተመርጧል፤ ደብረማርቆስ ከተማ የሚገኘው ንጉስ ተክለሃይማኖት አጠቃላይ ሁለተኛደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ደግሞ በአመቺ ንሞና ከተመረጠ በኋላ በዚህ ትምህርትቤት የሚገኙ የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች በዕጣ ተመርጠው ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ ክልሉ በዓላማተኮር ንሞና የተመረጠው ጥናቱ አፍፈት ተማሪዎች ላይ የሚያተኩር በመሆኑ ነው።ትምህርት ቤቱ በአመቺ ንሞና የተመረጠበት ምክንያትም ጥናቱ ከፊል ፍትነታዊእንደመሆኑ መጠን ትምህርት ቤቱን እና የአማርኛ ቋንቋ መምህራንን ልዩ ትብብር እናድጋፍ የሚፈልጉ ጉዳዮችን የሚጠይቅ በመሆኑ ለዚህም የትምህርት ቤቱ አስተዳደር፣መምህራንና ተማሪዎች ለጥናቱ ፈቃደኛ በመሆናቸው ነው፡፡ የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች በዕጣየተመረጡበት ምክንያት ደግሞ ከ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በስተቀር ጥናቱ በ9ኛ፣ 10ኛ እና11ኛ ክፍልተማሪዎች ላይ ቢካሄድ በተማሪዎች መረጃ የመሰብሰብ ሂደት ላይ ችግርአይኖርም ተብሎ ስለታሰበ ነው፡፡ መረጃዎች ከተሳታፊ ተማሪዎች በመጻፍ ችሎታ ፈተናእና በመጻፍ ተነሳሽነት የጽሑፍ መጠይቅ ተሰብስበዋል፡፡ የተገኙትመረጃዎችምየመተንተኛ ስልቱ እሙኖች በገላጭ ስታቲስቲክስ ከተፈተሹ በኋላ በሙከራና በቁጥጥርቡድኖች መካከል ልዩነት መኖር አለመኖሩን ለመፈተሽ የቅድመና ድኅረ ትምህርትአጠቃላይ የመጻፍ ችሎታ፣ ንዑሳን ችሎታዎች (ይዘት፣ አደረጃጀት፣ የቃላት አመራረጥናአጠቃቀም፣ የቋንቋ አጠቃቀም እና ስርዓተ አጻጻፍ) አማካይ ውጤቶችና የመጻፍ ተነሳሽነትየጽሑፍ መጠይቅ አማካይ ውጤቶች በባለብዙ ተላውጦ ልይይት ትንተና ዘዴ (Multivariate Analysis of Variance, MANOVA) ተሰልተው ተተንትነዋል፡፡ በተገኙትውጤቶች መሠረትም፣ የተማሪዎች አጠቃላይ የመጻፍ ችሎታ እና ንዑሳን ችሎታዎች(ይዘት፣ አደረጃጀት፣ የቃላት አመራረጥና አጠቃቀም፣ የቋንቋ አጠቃቀም እና ስርዓተአጻጻፍ) እንዲሁም የመጻፍ ተነሳሽነት የጽሑፍ መጠይቅ ውጤቶች የሙከራ ቡድንተማሪዎች ከቁጥጥር ቡድን ተማሪዎች አማካይ ውጤቶች ተሽለውና ጉልህ (p<.05) ልዩነት ያላቸው ሆነው ተገኝተዋል። በዚህም መሠረት ፕሮጀክት ተኮር መማር የተማሪዎችንአጠቃላይ የመጻፍ ችሎታ እና ንዑሳን ችሎታዎች እንዲሁም የመጻፍ ተነሳሽነት ለማሻሻልሚና እንዳለውና ሚናውም ከፍተኛ እንደሆነ ጥናቱ አሳይቷል፡፡ በመሆኑም፣ የመጻፍትምህርትን በፕሮጀክት ተኮር መማር ተግባራት ማቅረብ እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል፡፡
  • Item
    የየምወድሽ በቀለ ወልደገብርኤል የሕይወት ታሪክና ስራዎቿ
    (Addis Ababa University, 2024-06) ዙፋን ካሳው; ሙሐመድ አሊ (ዶ/ር)
    ‹‹የየምወድሽ በቀለ የሕይወት ታሪክና ስራዎቿ›› ጥናት በየምወድሽ በቀለ በስራና የሙያ የሕይወት ታሪክ ላይ ትኩረት አድርጓል፡፡ ጥናቱ በዋናነት ከጋዜጠኛነት ሙያ ጋር የተሳሰረችበትን አጋጣሚና የሰራችበትን የህይወት ጉዞ፣ ከድርሰት መጻፍ ጋር የተዋወቀችበትንና ድርሰቶቿ ከጋዜጠንነት ሙያዋ ጋር ያላቸውን ትስስር የሚመረምር ነው፡፡ ለዚህም ሲባል በአንድ በኩል ተጠኝዋን ግለሰብና ቤተሰብ እንዲሁም የቅርብ ጓደኞች ቃለመጠይቅ በማድረግ የህይወት ታሪኳ ክፍል መረጃ ተሰብስቧል፡፡ የሙያዋንና የድርሰት ስራዎቿን ትስስር ለመመርመርም ከህይወት ታሪኳ ጋር ትስስር ያላቸውን የድርሰት ስራዎች በጥልቅ ምንባብ ተመርጠዋል፡፡የምወድሽ በቀለ ከ1972 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ 2014 ዓ.ም.ድረስ አስር ረጅም እና አጫጭር ልቦለዶች፣የግጥም መድብሎችና የእውነተኛ ታሪኮች ስብስቦች አሳትማለች፡፡ከሌሎች ደራሲያን መድብሎች ጋር ደግሞ 6 አጫጭር ልቦለዶች ፣ግጥሞችና እውነተኛ ታሪኮች አሏት፡፡በጥናቱ በተመረጡት ልቦለዶች በግል ህይወቷና ከስራ አለም ከነበሯት ገጠመኞቿ ተነስታ በሴቶች ላይ እንደምታተኩር ፤በአፃፃፍ ስልት ደግሞ የወንጀል አፃፃፍን እንድትከተል ተፅእኖ አድርጎባታል::
  • Item
    በአማርኛ ቋንቋ ትምህርት የተማሪዎች የራስመር መማር ብልሃቶች አጠቃቀም፣ የማንበብ ግለብቃት እምነት እና አንብቦ የመረዳት ችሎታ ጾታ ተኮር ተዛምዶ፤ በተመረጡ የአስራአንደኛ ክፍል ተማሪዎች ተተኳሪነት
    (Addis Ababa University, 2024-06) ይድነቃቸው ገረመው ዓለሙ; ገረመው ለሙ (ዶ/ር); ሰይድ ይመር (ዶ/ር)
    በአማርኛ ቋንቋ አንብቦ የመረዳት ችሎታ፣ የማንበብ ግለብቃት እምነትና የራስመር መማር ብልሃቶች አጠቃቀም መካከል ያለውን ተዛምዶ መፈተሽ የዚህ ጥናት ዋና ዓላማ ነው፡፡ የተዛምዶ ፍተሻውን ለማድረግ ጥናቱ ተዛምዷዊ የምርምር ንድፍን የተከተለ ሲሆን በአዲስ አበባ አስተዳደር በሁለት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚማሩ የአማርኛ ቋንቋ አፍፈትየሆኑ የአስራአንደኛ ክፍል ተማሪዎች እኩል እድል ሰጭ ንሞና ዘዴ በመጠቀም የጥናቱ ተሳታፊ እንዲሆኑ ተመርጠዋል፡፡ የአንብቦ መረዳት ችሎታ መለኪያ ፈተና፣ የማንበብ ግለብቃት እምነት መጠይቅ እና የራስመር መማር ብልሃቶች አጠቃቀም መጠይቅ በመጠቀም ለጥናቱ የሚያስፈልጉ መረጃዎችን መሰብሰብ ተችሏል፡፡ የተሰበሰበው መረጃ ከተጠናቀረ በኋላ ገላጭና ተንባይ ስታትስቲክሳዊ ዘዴዎችን በመጠቀም ለጥናቱ ጥያቄዎች መልስ ለማግኘት የሚያስችል የመረጃ ትንተና ተካሂዷል፡፡ ከመረጃ ትንተናው በተገኘው ውጤት መሰረትየ11ኛ ክፍል አማርኛ ቋንቋ አፍፈት ተማሪዎች አንብቦ የመረዳት ችሎታ በምን ደረጃ ላይ እንደሆነ ለሚጠይቀው የጥናቱ ጥያቄ የፈተናው አማካይ ውጤት(56.65%) እና የውጤት ስርጭቱ አብዛኞቹ ተማሪዎች አንብቦ የመረዳት ችሎታቸው መካከለኛ እንደሆነ አሳይቷል፡፡ ጾታ በተላውጦዎቹ ላይ ያሳየውን ልዩነት ለማወቅ በተደረገ የቲ ቴስት ፍተሻ ውጤት መሰረት ጾታ በራስመር መማር ብልሃቶች አጠቃቀም ላይ ብቻ ጉልህ ልዩነት ሲፈጥር በአንብቦ መረዳት ችሎታና በማንበብ ግለብቃት እምነት ላይ ጉልህ ልዩነት አልፈጠረም፡፡ በተላውጦዎቹ መካከል ተዛምዶ መኖሩን ለመፈተሽ በተካሄደ የፒርሰን ተዛምዶ ትንተና መሰረት በአስራ አንደኛ ክፍል አማርኛ ቋንቋ አፍፈት ተማሪዎች አንብቦ የመረዳት ችሎታ እና በራስመር መማር ብልሃቶች አጠቃቀም መካከል ተዛምዶ አለመኖሩ(r=.135) ተረጋግጧል፡፡ በአንብቦ የመረዳት ችሎታ እና በማንበብ ግለብቃት እምነት(r=.263) እንዲሁም በራስመር መማር ብልሃቶች እና በተማሪዎች የማንበብ ግለብቃት እምነት መካከል(r=.575) አዎንታዊ ተዛምዶ ተገኝቷል፡፡ በመጨረሻም የጥናቱን ውጤት መሰረት በማድረግ አስተያየቶች ተጠቁመዋል፡፡
  • Item
    የፅህፈት ችልታ ንፅፅራዊ ጥናት በሀድይኛና በስልጥኛ ቋንቋ አፋቸውን ፈትተው፣አማርኛን እንደሁለተኛ ቋንቋ በመማር ወደዘጠነኛ ክፍል በገቡ ተማሪዎች ተተኳሪነት
    (Addis Ababa University, 2023-08) ፀጋነሽ አየለ አያኖ; ግርማ ገብሬ(ድ/ር)
    የዚህ ጥናት ዋና ዓሊማ በሀድይኛ እና በስልጥኛ ቋንቋ አፊቸውን ፈትተው አማርኛን እንደሁለተኛ ቋንቋ ተምረው ወደ ዘጠነኛ ክፍል የገቡ ተማሪዎች የፅህፈት ችልታ ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ እና የትኞቹ የተሻለ የፅህፈት ችሎታ እንዳላቸው በንፅፅር መመርመር ነው፡፡ ጥናቱም በሁለት ቡድኖች መካከል ያለውን የመጻፍ ችሎታ በንጽጽር ስለሚፈትሽ አወዳዳሪ ንድፍ ተግባራዊ ያደረገ ሲሆን፣መጠናዊና አይነታዊ የምርምር ዘዴን የተከተለ (Mixed approach) ነው፡፡ ይህ ጥናት የተካሄደው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀድያ ዞን በአንሌሞ ወረዳ ከሚገኙ አምስት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ በአጫሞ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ብቻ ነው፡፡ ከእነዚህ ትምህርት ቤቶች በ2015 ዓ.ም በ9ኛ ክፍል በመማር ያለ ተማሪዎች በዚህ ጥናት ተሳትፈዋል፡፡ የጥናቱ መረጃዎችም በመጻፍ ችሎታ ፈተናና ለተማሪዎች ከተሰራጨ የጽሁፍ መጠይቅ የተሰበሰቡ ሲሆን፣የትንተናውም ውጤት በማወዳደር ስልት ተብራርቷል፡፡ የጥናቱም ውጤት በሀድይኛ እና በስልጥኛ ቋንቋ አፈ-ፈት የሆኑ ተማሪዎች የተለያየ ችሎታ ያላቸው መሆኑን አመልክቷል፡፡ ከሆሄያትና ቃላት አጠቃቀም አኳያ የስልጥኛ ቋንቋ አፍ-ፈት ተማሪዎች የተሻለ ሲሆኑ፣ከአረፈተ ነገር አወቃቀር እና ከአንቀጽ አደረጃጀት አኳያ በሀድይኛ ቋንቋ አፈ-ፈት የሆኑ ተማሪዎች ተሽለው መገኘታቸውን የጥናቱ ውጤት አረጋግጧሌ፡፡ ከስርዓተ ነጥቦች አጠቃቀም አኳያ በሀድይኛ እና በስልጥኛ ቋንቋ አፍ-ፈት የሆኑ ተማሪዎች ተመሳሳይ ችሎታ ያላቸው መሆኑ ተመልክቷል፡፡ እንዱሁም ተማሪዎች በአማርኛ ቋንቋ ሇመጻፌ ያሊቸው ፌሊጎትና ችልታቸው የተቀራረበ ሲሆን፣ መምህራን ተማሪዎችን በአማርኛ ድርሰት በመጻፍ ሂደት ለማብቃት ያላቸው ሚና መካከለኛ መሆኑ ተረጋግጧሌ፡፡ በተጨማሪ በሀድይኛ እና በስልጥኛ ቋንቋ አፍ-ፈት የሆኑ ተማሪዎች ለመጻፍ ያላቸው ችሎታ ደካማ መሆኑንም የጥናቱ ውጤት አመልክቷል፡፡ ስለሆነም የአማርኛ ቋንቋ መምህራን በመማሪያ ክፍል ውስጥና ከመማሪያ ክፍል ውስጥ በሚሰሩት ተግባራ የተማሪዎችን የመጻፍ ችሎታ ማሻሻል ላይ ልያተኩሩ ይገባል
  • Item
    የማንበብና የመፃፍ ክሂሎችን አቀናጅቶ ማስተማር ክሂሎችን ለማሻሻል ያለው ሚና ትንተና (በጉራጌ ዞን በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ 9ኛ ክፍል ተማሪዎች ተተከሪነት)
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስት, 2016-11) ለምለም ከበደ; ዳዊት ፍሬህይወት (ዶ/ ር )
    የዚህ ጥናት ዋና ዓላማ በጉራጌ ዞን በገደባኖ ሁለተኛ ደረጃ ትምህረት ቤት የማንበብና የመፃፍ ክሂሎችን አቀናጅቶ ማስተማር ክሂሎችን ለማሻሻል ያለው ሚና መተነን ነው። የጥናቱ የአጠናን ዘዴ ቅይጥ የምርምር ዘዴ ሲሆን በዋናነት አይነታዊ ምርምርና በደጋፊነት ደግሞ መጠናዊ ምርምር ዘዴን አካቷል፡፡ የጥናቱ ሂደትም ተግባራዊ ይሆን ዘንድ አስፈላጊ መረጃዎችን ለመሰብሰብ የክፍል ውስጥ ምልከታ፣ ለተማሪዎች የቅድመና የድህረ ትምህርት ፈተና እና ቃል መጠይቅ ፤ ለመምህራን ደግሞ በቃለ-መጠይቅ መረጃ ተሰብስባል፡፡ የተገኙት መረጃዎችም በሰንጠረዥ ተደራጅተው በቁጥርና በመቶኛ ተተንትነው ቀርበዋል፡፡ እንዲደዚሁም በቃል መጠይቅ የተገኙ መረጃዎችም በምልከታ ለተገኙ መረጃዎች አጋዥ ሆነው ተተንትነዋል፡፡ የመከራ ቡድኖቹም ቅድመ ትምህርት ፈተና ተፈትነዋል። ለእንድ ወር በእቅድ የተደገፍ ትምህርት ተምረው ድህረ ህርት ፈተና ተፈትናዋል። በቡድኖቹ መካከል ያለውን ልዩነት ለማረጋገጥ የፈተናእ ውጤት በአማካይ ተስልቶ ተነፃፅሯል ። ከተማሪው የተገኘው ቃለ መጠይቅምላሽና ክንውን ምልከታው ተመሳሳይነት አረጋግጧል ።ሰለዚህ የማንበብና ይመፃፍ ክሂሎች ካላችው ትስስርና ዝምንድና አንፃር በተናጥል ከመቅረብ ይልቅ በቅንጅት ቢቀርብ ለክሂሌችን መጒልበት የላቀ እንደሆነ ጥናቱ አሳይቷል።በመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያዎች አመካይነት በተገኘ የውጤት ትንተና መሰረትም መምህራን የማንበብና የመፃፍ ክሂልን በቅንጅት ለማስተማር እየተገበሩት ያለው አካሄድ ክሂሎቹን ለማቀናጀትና ለማዳበር ያላቸው ሚና ዝቅተኛ እንደሆነ መምህራን ከተማሪዎች ችሎታ፣ ዳራና ፍላጎት ጋር የተጣጣሙ ይዘቶች፲ን እንደማያቀርቡ፣ ከመማሪያ መጽሀፍ በተጨማሪ ለዓላማው ተስማሚ የሆኑ አጋዥ መሳሪያዎችን እንደማይሰጡ ተረጋግጧል፡፡ የመማሪያ መጽሐፍ የማንበብና የመፃፍ ክሂልን በቅንጅት ለማቅረብ አመቺ እንደልሆነና ለ፸፻መምህራን ስለኪሂሎች ቅንጅታዊ አቀራረብ አጫጭር ስልጠናዎችንና ዋረክሽፖችን አለሰመስጠት ተፅእኖ እንዳሳደረባቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡ የተገኘው የትንተና ውጤት እንደሚያሳየው የማንበብና የመፃፍ ክሂልን በቅንጅት ማስተማር ዘዴ በዝቅተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ተመላክቷል፡፡
  • Item
    ከ2013-2014ዓ.ም የአማርኛ ቋንቋ ማጠቃለያ ፈተናዎች የይዘት ተገቢነት ግምገማ በጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ በየዋኸንየ አጠ/2ኛ/ደ/ እና መሰናዶ ትምህርት ቤት በዘጠነኛ ክፍል ተተኳሪነት
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርሲት, 2016-12) ሞገስ አዲስ; ፕሮፈፌሰር ጌታሁን አማረ
    የዚህ ጥናት አሊማ በጉራጌ ዞን በእዣ ወረዲ በየዋኸንየ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለዘጠነኛ ክፍል ተዘጋጅተው የቀረቡ አማርኛ ቋንቋ የማጠቃለያ ፈተናዎችን የይዘት ተገቢነት መገምገም ነው፡፡ ጥናቱ አይነታዊ የአጠናን ዘዴን የተከተለ ሲሆን ገምጋሚ የምርምር ንድፍን መሰረት አድርጎ ተሰናድቷል፡፡ የንሞና አመራረጡ አመቺ ስልትን የተከተለ ነው፡፡በፈተና የሰነድ ፌተሻ የመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያነት የተገኙትነን መረጃዎች መተንተን ተችሎል፡፡ ትንተናዎቹም በገለጻዊና በትረካዊ መልክ ቀርበዋል፡፡፡፡ የጥናቱ ግኝቶችም እንደሚያሳዩት የተዘጋጁት ምዘናዎች የተማሪዎችን የቋንቋ ችሎታ በሚገባ የማይመዝኑ፣የአደረጃጀት ችግር ያለባቸው፣አውዳዊ ያልሆኑ፣ መስፈርቶች ያልተዘጋጁላቸው፣ ከችሎታ መለኪያ ፈተና አዘገጃጀት መርሆዎች አንፃር ውስንነት ያለባቸው እንደሆኑ መረጃዎቹ አመሊክተዋል፡፡ ስለሆነም የሚዘጋጁት የቋንቋ ፈተናዎች ከመርሃ ትምህርቱና መማሪያ መፅሀፈ ጋር ያላቸው ትስስር የተሻለ ቢሆንም ሁለንም የቋንቋ ትምህርት ይዘቶች በትክክሌ አካቶ ከማቅረብ አንፃር፣ የተመረጡት የይዘቶች ተገቢነት፣ አደረጃጀት፣ ነጠላ ከመሆን፣ በአውድ ከመቅረብ፣ ከማሳሳት ሀይሌ፣ በጥያቄዎቹ ግንድ ላይ ከመቅረብ፣ ሁለን አካታች ከመሆን፣ ካልቸው የቁጥብነት ሁኔታ፣ ውስንነቶች እንዲለባቸው መደምደሚያ ላይ የተደረሰ ሲሆን የቀጣይ የመፌትሄ ሃሳቦችም ተቀምጠዋል፡፡
  • Item
    የድጋፍ ብልሃቶች በአንብቦ የመረዳት ችሎታ እና ግለመር ማንበብ ላይ ያላቸው ተፅዕኖ፤ በ7ኛ ክፍል ተማሪዎች ተተኳሪነት
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ, 2016-10) ራሔል ሲሳይ ተገኘ; ተባባሪ ፕሮፌሰር ተስፋየ ሸዋየ
    የዚህ ጥናት ዓላማ የድጋፍ ብልሃቶች የተማሪዎችን በአማርኛ ቋንቋ አንብቦ የመረዳት ችሎታ እና ግለመር ማንበብ ላይ ያላቸውን ተፅዕኖ መፈተሸ ነበር፡፡ ጥናቱ በዓይነቱ ቅደምተከተላዊ ቅይጥ (በአመዛኙ መጠናዊ) ሲሆን ቅድመና ድህረ ትምህርት ባለቁጥጥር ቡድን ፍትነት መሰል ንድፍን የተከተለ ነው፡፡ በ2015 ዓ.ም በአዲስአበባ ከተማ አስተዳደር፣ በጉለሌ ክፍለ ከተማ በአዲስተስፋ አንደኛ ደረጃ ትምህርትቤት የ7ኛ ክፍል ተማሪዎች ተሳትፈዋል፡፡ መረጃዎችን ለመሰብሰብም አንብቦ የመረዳት ችሎታ ፈተናና የግለመር ማንበብ መጠይቅ ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡ ሌላው በአጋዥነት ድህረቡድን ተኮር ውይይት ተግባራዊ ሆኗል፡፡ እንዲሁም ሁለቱ ቡድኖች በተቀመጠላቸው የማስተማሪያ መንገድ መማራቸውን ለማረጋገጥ ሲባል ምልከታ ተካሂዷል፡፡ በቅድመ ፈተናና በቅድመ የጽሑፍ መጠይቅ የተገኙ ውጤቶች በጥንድና ነፃ ቲ-ትስቶች የትንተና ስልት እንዲሁም በድኅረ ፈተናና በድኅረ የጽሑፍ መጠይቅ የተገኙ ውጤቶች በጥንድ፣ ነፃ ቲ-ትስቶችና በአበር ልይይት ትንተና ስልቶች ተተንትነዋል፡፡ በተጨማሪም ከድህረቡድን ተኮር ውይይት የተገኙ አይነታዊ መረጃዎች በጭብጥ ትንተና ዘዴ ተተንትነዋል፡፡ ከትንተናው የተገኙት ውጤቶችም እንደሚያመለክቱት በቅድመፈተናና በቅድመየጽሑፍ መጠይቅ ቡድኖች ተመጣጣኝ አማካይ ውጤቶች ያስመዘገቡ ሲሆን፤ በድኅረ ፈተና አንብቦ የመረዳት ችሎታና አንብቦ የመረዳት ንዑስ ክሂሎች፣ በድኅረ የጽሑፍ መጠይቅ ግለመር ማንበብ የሙከራ ቡድኑ ተማሪዎች ከቁጥጥር ቡድኑ ተማሪዎች ጉልህ የሆነ ልዩነት አሳይተዋል (P= <0.05)፡፡ ይህም ውጤት በድጋፍ ብልሀቶች መማር የተማሪዎችን አንብቦ የመረዳት ችሎታና ግለመር ማንበብን ከማሻሻል አኳያ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቁሟል፡፡ በተገኙት ውጤቶች በመመስረት የመፍትሄ ሀሳቦችና የጥናት ጥቆማዎች ተሰጥተዋል
  • Item
    የአንብቦ መረዳት ክሂል ፍተሻ፤ በፓዊ ወረዳ የፓዊ መሰናዶ ትምህርት ቤት በ9ኛ ክፍል ተማሪዎች ማሳያነት
    (አድስ አባባ ዩኒቨርሲት, 2016-12) ወርቅነህ ይርጋ ደምሴ; ግርማ ገብሬ (ድ/ር)
    የዙህ ጥናት ዋና ዓሊማ በፓዊ ወረዳ የፓዊ መሰናዶ ትምህርት ቤት የዘጠነኛ ክፍል ተማሪዎች በአማርኛ አንብቦ የመረዳል ክሂል ደረጃን መመርመር ነው፡፡ የጥናቱ ንድፍ ከመጠናዊ ምርምር የሚመደብ ሲሆን ገሊጭ የምርምር ስልትን ተከትሎ ተካሂዶል፡፡ ጥናቱ ፓዊ መሰናዶትምህርት ቤት በአመቺ ንሞና ዘዴ፣ የ዗ጠነኛ ክፍል ተማሪዎች በዓላማ ተኮር የንሞና ንሞና ዘዴ እንዲሁም ተጠኚ ሶስት መማሪያ ክፍሎችን በእጣ (በልተሪ) ንሞና ዘዴ በመምረጥ ተማሪዎችን በመረጃ ምንጭነት አካቷል፡፡ አጥኚው የዘጠነኛ ክፍል ተማሪዎች በአማርኛ አንብቦ መረዳት ችሎታ ለመለካት የአንብቦ መረዳት ፈተና፣ የንባብ ትምህርት አተገባበርን ለመፈተሸ ክፍል ውስጥ ምልከታ እና ቃለ መጠይቅ ተጠቅሟል፡፡ በጥናቱ ውጤት መሰረትም በጥናቱ የተሳተፉ 194 ተማሪዎች በመጀመሪያው ፈተና (የሚጠበቅ ውጤት 18.75፣ የተመዘገበ አማካይ ውጤት 14.19)፣ በሁለተኛዉ ፈተና (የሚጠበቅ ውጤት 18.75፣ የተመዘገበ አማካይ ውጤት 14.71) በአጠቃላይ ፈተና ውጤት ደግሞ (የሚጠበቅ ውጤት 37.50፣ የተመዘገበ አማካይ ውጤት 28.90) ሆኖ ተመዜግቧል፡፡ ይህም የተመዘገበው በአማርኛ አንብቦ የመረዳት አማካይ ውጤት ከሚጠበቀው ውጤት እንደሚያንስ (ዜቅተኛ መሆኑን) ያመለክታል፡፡ በጥናቱ የተሳተፉ 99 ወንድ እና 95 ሴት በድምሩ 194 የዘጠነኛ ክፍል ተማሪዎች አማካይ ውጤት በአጠቃሊይ አንብቦ መረዳት ፈተና ወንድ ተማሪዎች 30.0606 እና ሴት ተማሪዎች 27.6947 ሆኖ ተመዜግቧል፡፡ በተመሳሳይ የባዕድ ናሙና ቲ-ቴስት (Independent Sample t-test) ስታትስቲክስ ውጤት ማየት እንደሚቻለዉ ተጠኚ ተማሪዎች ባስመዘገቡት አጠቃላይ በአማርኛ አንብቦ የመረዳት አማካኝ ውጤትና በሚጠበቀው ውጤት መካከል ያለዉ የልዩነት ጉልህነት ደረጃ የወንድ ተማሪዎች t(98) = 2.393 P<0.018 እንዲሁም የሴት ተማሪዎች t(94) = 2.405 P<0.017 ሆኖ ስለተገኘ ከመቁረጫ ነጥብ (0.05) አንሷል፡፡ ይህም በአማርኛ አንብቦ የመረዳት ችሎታ በወንዶችም በሴቶችም ተማሪዎች የተመዘገበው አማካይ ውጤት ከሚጠበቀው ውጤት በታች (ዝቅ ብሎ) ሆኖ መገኘትና ከሴቶች ይልቅ ወንዶች የተሻለ ውጤት ማስመዜገባቸዉ በስታስቲክስ ጉልህ (ተቀባይነት ያለዉ) መሆኑን ያመለክታል፡፡ በምሌከታ በተገኘዉ ዉጤት መሰረት ተጠኚ መምህራን በቅድመ ንባብ እና በንባብ ጊዜ ተግባራት ላይ ጥቂት ድክመቶች (ወጣገባነት) የተስተዋለባቸው ቢሆንም እንደ አጠቃሊይ ሲታይ ጠንካራ (የተሻለ) መሆናቸዉ ተረጋግጧል፡፡ በተቃራኒው በደህረ ንባብ ትምህርት ተግባራት ደረጃ በጣም ደካማ መሆናቸው ተረጋግጧል፡፡ በመጨረሻም አጥኝው የጥናቱን ግኝት መሰረት በማድረግ የመፍትሄ ሃሳቦችን ጠቁሟል፡፡
  • Item
    አንብቦ መረዳትና የመፃፍ ክሂል ቅንጅታዊ አቀራረብ ትንተና (በጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ በጢያ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ9ኛ ክፍል መምህራን ተተኳሪነት)
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ, 2016-12) ወንዱ ፀጋ; ተስፋዬ ሸዋዬ
    የዚህ ጥናት ዋና ዓላማ በጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ በጢያ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ9ኛ ክፍልአራት አማርኛ ቋንቋ መምህራን ትኩረቱን በማድረግ የአንብቦ መረዳትና የመፃፍ ክሂሎችን ቅንጅታዊ አቀራረብ መተንተን ነው፡፡ የዓላማውን ውጤት ለማስገኘትም ቃለ መጠይቅና ምልከታ መረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያ በመሆን አገልግለዋል፡፡ በዚህም አጥኚው ተምህርት ቤትን በአመቺ(የግኝት) ናሙና፣ የክፍል ደረጃን በወሳኝ ናሙና ፣ መምህራንን በጠቅላይ ንሙና ዘዴ መርጧል።በአራት ተተኳሪ የአማርኛ ቋንቋ መምህራን በክፍል ውስጥ በመገኘት ለአራት መማሪያ ክፍሎች ለእያንዳንዱ ሁለት ሁለት ምልከታ በማድረግና ለአራት መምህራን ቃለ መጠይቅ በማድረግ መረጃዎች ተሰብስበዋል። በእነዚህ መሳሪያዎች የተሰበሰቡት መረጃዎች ተተንትነው ውጤታቸው ተግምግሟል። ከጥናቱ ዓላማ በመነሳት በሚከተለው መልኩ ጥናቱን በማጠቃለል ማቅረብ ተችሏል፡፡ መምህራን የማብራራትና መተርጎም፣ መተንበይና መገመት፣ ጥያቄ የመጠየቅ እና የማጠቃለል ብልሃቶችን እየቀያየሩ ለመጠቀም እንደሚሞክሩ ነው ከቃለ መጠይቁ መረዳት የተቻለው። አንብቦ የመረዳትንና የመጻፍን ክሂሎችን አቀናጅቶ መስጠት ግን የሁለት ክሂሎችን ችሎታ እንደሚያጎናጽፍ ጥናቱ አረጋግጧል። በመሆኑም ለተማሪዎች ክሂሎች በተናጠል ከሚቀርቡ ይልቅ አንብቦ መረዳትና መጻፍ፣ ማዳመጥና መናገር ክሂሎች እየተቀናጁ እንዲማሩ እንድማሩ ቢደረግ የሚል አቅጣጫ ጥናቱ አስቀምጧል፡፡ እንዲሁም የማስተማሪያ ስልቶችን እየቀያየሩ መጠቀም ተማሪዎች ተነሳሽነት እንዲኖራቸው የሚያደርግ እንደሆነ ጥናቱ የመላክታል።ስለዚህ መምህራን አንብቦ የመረዳትና መጻፍ ክሂሎችን አቀናጅተው ሲያስተምሩ በየትኛው ስልት ማቅረብ እንዳለባቸው ወስነው መቅረብ አለባቸው፡፡ ከቀረቡት የጥናቱ ግኝቶች በመነሳትም ቀጥለው የሚቀርቡት የመፍትሔ ሃሳቦች ቀርበዋል፡፡ መምህራን አንብቦ የመረዳትና የመጻፍ ክሂሎችን በቅንጅት በሚያቀርቡበት ወቅት በቅንጅት የሚቀርቡበትን ዓላማ በመናገር ቢጀምሩ፣ አንብቦ መረዳትንና የመጻፍ ክሂልን ሲስተምሩ የማስተማሪያ ዘዴያቸውንና የአቀራረብ ስልታቸውን ከማስተማራቸው በፊት ወስነው ቢቀርቡ፤ መምህራን የማብራራትና መተርጎም፣ መተንበይና መገመት፣ ጥያቄ የመጠየቅ እና የማጠቃለል ብልሃቶችን እየቀያየሩ ለመጠቀም እንደሚጠቀሙ ከጥናቱ ውጤት መረዳት ይቻላል። ስለዙህ ክሂሎችን በተናጠል ከማስተማር ልምድ ወጥተው አንብቦ መረዳትንና መጻፍን አቀናጅተው ቢያሰተምሩ በአንድ የትምህርት ክፍለ ጊዜ ሁለት ክሂሎችን በማስተማር የአንብቦ መረዳትና መፃፍ ችሎታዎችንና ተግባቦቶችን ለተማሪዎች የሚያጎናጽፍ መሆኑን ይህ ጥናት ያሳያል
  • Item
    “ሊሚናሊቲ” እና ለውጥ በሕይወት ሽግግር ሥርዓቶች በጃቢ ጠህናን ማኅበረሰብ
    (Addis Ababa University, 2016-07) ሥራዬ እንዳለው ውበቴ; ዋልተንጉሥ መኮንን (ዶ/ር); ደስታ አማረ (ዶ/ር)
    ይህ ጥናት “ሊሚናሊቲ እና ለውጥ በሕይወት ሽግግር ሥርዓቶች በጃቢ ጠህናን ወረዳ ማኅበረሰብ” በሚል ርዕስ ተካሂዷል፡፡ በዋናነት ሊሚናሊቲንና ለውጥን ከሕይወት ሽግግር (ወሊድ፣ ጋብቻና ሞት) ሥርዓተ ክዋኔዎች ጋር አያይዞ አጥንቷል፡፡ የሕይወት ሽግግሮች በአንድ በኩል የግለሰብ በሌላ በኩል የጋራ ጉዳዮች በመሆናቸው ከሽግግሮች ባሕርይና ከማኅበረሰቡ ባህል ጋር በተያያዙ ምክንያቶች አስጊና አሳሳቢ፣ ባለጉዳዮችንም ለልዩ ልዩ ለውጦች የሚያጋልጡ ናቸው፡፡ በመሆኑም በሕይወት ሽግግሮች ወቅት የተለያዩ ሥርዓተ ክዋኔዎች ይፈጸማሉ፡፡ ጥናቱ እነዚህን ሥርዓተ ክዋኔዎች ሽግግሩን ከሚያካሂዱ ባለጉዳዮች ጋር በማስተሳሰር፣ በዐማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት፣ በምዕራብ ጎጃም ዞን፣ በጃቢ ጠህናን ወረዳ የኦርቶዶክስ ክርስትና ሃይማኖት ተከታይ ማኅበረሰብ እምነትና ባህል ማሳያነት አጥንቷል፡፡ የሕይወት ሽግግሮች ባለጉዳይን አስጨናቂ ያደረጉባቸውን ሁኔታዎች መለየት፤ በወቅቱ የሚከወኑ ሥርዓቶችን ዓላማ መግለጽ፤ ሽግግሩ ያስከተላቸውን ለውጦች መፈተሽ፣ በሽግግሩ ከተገኙ ለውጦች ጋር የሚያስተዋውቁ ወይም የሚያላምዱ ብልሃቶችን መመርመር እና በሕይወት ሽግግር ሥርዓቶች ላይ የተገለጡ የጋራ ትዕምርቶችን መተንተን የሚሉ ዓላማዎችን አሳክቷል፡፡ ጥናቱ ዓይነታዊ ሲሆን መረጃዎች ከቀዳማይና ከካልዓይ ምንጮች ተሰብስበዋል፡፡ ምልከታ፣ ቃለ መጠይቅ እና ተተኳሪ የቡድን ውይይት መረጃዎች የተሰበሰቡባቸው ዘዴዎች ሲሆኑ በሂደት አራት ዙር የመስክ ሥራ ተከናውኗል፡፡ በወረዳው ከሚገኙ አርባ አንድ ቀበሌዎች ውስጥ በዓላማ ተኮር የናሙና አመራረጥ ስልት ሥድስት ቀበሌዎች ተጠኝ ሆነው ተመርጠዋል፡፡ ለጥናቱ መረጃ በመስጠት ሠላሳ አምስት ሰዎች የተሳተፉ ሲሆን ከእነዚህ መካከል አስራ አራቱ በቁልፍ መረጃ ሰጪነት ተሳትፈዋል፡፡ አመራረጡም ጾታን፣ ማኅበራዊ ደረጃን፣ እድሜን፣ ለጉዳዩ ያለን ተጋላጭነት እና ሀሳብን የመግለጽ ብቃት ከግምት ውስጥ ያስገባ ነው፡፡ መረጃው በዲጅታል ካሜራ፣ በመቅረጸ ድምጽ እና በማስታወሻ ደብተር ተይዟል፡፡ ትክክለኛነቱም መረጃ ሰጪዎች በተደጋጋሚ ያነሷቸው፣ በምልከታ ወቅት ያጋጠሙ እና በተተኳሪ የቡድን ውይይት ወቅት ተወያይተው የተስማሙባቸው ጉዳዮች መሆናቸውን በመለየት ተመሳክሯል፡፡ ከመረጃ ሰጭዎች የተገኙ መረጃዎች ትዕምርታዊ መስተጋብር፣ ተግባራዊ መዋቅራዊ እና ፍካሬ ልቡናዊ ንድፈ ሀሳቦች እንደ አስፈላጊነታቸው ለትንታኔ ማሕቀፍነት ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡ የመረጃ ትንተናው እንደሚያሳየው የጃቢ ጠህናን ወረዳ ማኅበረሰብ ከሃይማኖቱ፣ ከእምነቱ እና ከባህሉ የወጡ በርካታ ባህላዊ እሴቶች ባለቤት ነው፡፡ የሰውን ልጅ ስጋዊ አፈጣጠርና ባሕርይ ከመሬት አፈጣጠር ጋር፤ መንፈሳዊ አፈጣጠሩን ደግሞ ከነፋስ፣ ከእሳት ከውሃ እና ከመሬት ባሕርያት ጋር ያዛምዳል፡፡ በሌላ በኩል የሰው ልጅ ልባዊት (ሀሳብ)፣ ነባቢት (ንግግር) እና ህያዊት (ዘላለማዊነት/ትንሳኤ)፣ የተባሉ የመንፈሳዊ ሰብዕና መገለጫዎች ወይም ባሕርያተ ነፍስ አሉት ብሎ ያምናል፡፡ የጃቢ ጠህናን ወረዳ ማኅበረሰብ እርስ በእርሱ እንዲተሳሰርና እንደ ማኅበረሰብ እንዲቀጥል ያስቻሉ የተለያዩ የዝምድና መፍጠሪያ እና አብሮ የመኖር ብልሃቶች አሉት፡፡ የሕይወት ሽግግሮች ባለጉዳዩን የደረጃ ሽግግር እና ለውጥ እንዲያካሂድ የሚያደርጉ መሆናቸው፤ ከሽግግሮች ጸባይ እና ከማኅበረሰቡ ባህል በሚነሱ ምክንያቶች ዋናው የሽግግር ወቅት አስጊ እና አሳሳቢ መሆኑን አሳይቷል፡፡ ከዚህም የተነሳ የሕይወት ሽግግሮች አዲስ እና መለማመጃ የሌላቸው፣ ድንገት ደራሽ፣ ቅጽበታዊ፣ ምሥጢራዊ፣ ራሳቸውን የማይደግሙ፣ አስገዳጅ እና ነጣይ በመሆናቸው ባለጉዳዮችንም ሆነ ማኅበረሰቡን ለጭንቀትና ለግራ መጋባት ይዳርጋሉ፡፡ በወቅቱ የተፈጠረን ጭንቀት እና ግራ መጋባት ለመቀነስ ወይም ለማከም የተለያየ ዓላማና ሚና ያላቸው ሥርዓተ ክዋኔዎች ከቅድመ ሽግግሩ ጀምሮ ዋናው ሽግግር ከተካሄደ በኋላም ይፈጸማሉ፡፡ የሕይወት ሽግግሮች ባለጉዳዮች የስም፣ የአለባበስና የአጊያጊያጥ፣ የቋንቋ አጠቃቀም፣ የማኅበራዊ ደረጃና የስነ ልቡና ለውጥ የሚያካሂዱባቸው መሆናቸውን እና ከእነዚህ ለውጦች ጋር የሚያስተዋውቁ እና የሚያለማምዱ ክዋኔዎችን አሳይቷል፡፡ በሕይወት ሽግግር ሥርዓቶች ወቅት ከተገለጡ የጋራ ትዕምርቶች መካከል ቀዳሚን ማክበር፣ ጀግናን ማወደስ፣ ሃይማኖትን፣ ሀገርን እና ሥራን መውደድ፣ መልካም ምግባር ማኅበረሰቡ በተለመደው መልክ እንዲቀጥል ያገዙ ዋና ዋና መልካም እሴቶች ናቸው፡፡
  • Item
    የሰዋስው ይዘቶች አቀራረብ እና አደረጃጀት ትንተና (በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በ2015 ዓ.ም.፣ ለ7ኛ እና ለ8ኛ ክፍል በተዘጋጁት የአማርኛ መማሪያ መጻሕፍት ተተኳሪነት)
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2024-08) ሙሉ ደርቤ; ጌታሁን አማረ (ፕ/ር)
    የዚህ ጥናት ዐቢይ ትኩረት በ2015 ዓ.ም. በአማራ ክልል ስራ ላይ በዋሉት የ7ኛ እና የ8ኛ ክፍል መማሪያ መጻህፍት ውስጥ የሰዋስው ይዘቶች አቀራረብና አደረጃጀት ትንተና ነው፡፡ የጥናቱ ዝርዝር ዓላማዎችም በመማሪያ መጻህፍቱ ውስጥ የተካተቱ የሰዋስው ይዘቶች የአቀራረብ መርሆዎችን ተከትለው መቅረባቸውን፣ የሰዋሰው ይዘቶቹ የአደረጃጀት መርሆዎችን ተከትለው መቅረባቸውን መተንተን እና በመጻህፍቱ ውስጥ ምን ምን ሰዋስዋዊ ይዘቶች እንደቀረቡ መፈተሽ የሚሉት ናቸው፡፡ የጥናቱ ዋና የመረጃ ምንጮች የመማሪያ መጻኅፍቱ ናቸው፡፡ በተጨማሪም በቃለ-መጠይቅ መረጃውን ለማጠናከር ተሞክሯል፡፡ የተሰበሰበው መረጃ በአይነታዊ ወይም በገላጭ የምርምር ዘዴ ተተንትኗል፡፡ በዚህም መሰረት በተተኳሪ መጻህፍቱ ውስጥ የቀረቡ የሰዋስው ይዘቶች አቀራረብ፣ ከግልፅነት፣ ከትክክለኛነት፣ ከተመጣጣኝነትና ከተገቢነት አንጻር ትተንትኗል፡፡ እንዲሁም የሰዋሰው ይዘቶቹን አደረጃጀት፣ከተከታታይነት፣ከተለጣጣቂነት፣ከዝርዝር ወደ አጠቃላይ፣ ከአጠቃላይ ወደ ዝርዝር አንጻር ያላቸው ገጽታ ምን እንደሚመስል ተፈትሷል፡፡ ይህን ለማሳካትም ጥናቱ በመማሪያ መጻህፍቱ ውስጥ የቀረቡ የሰዋስው ይዘቶች አቀራረብና አደረጃጀት በክለሳ ድርሳናት ከቀረቡ ጽንሰሀሳቦች አንጻር እየታዩ የተተነተኑ ሲሆን፣ በናሙናነት ከተመረጡ መምህራን በቃለ-መጠይቅ በተገኙ ምላሾች ትንተናውን ለማጠናከር ተሞክሯል፡፡ በመሆኑም የሰዋስዋዊ ይዘቶቹን አቀራረብ በሚመለከት መማሪያ መጻህፍቱ ውስጥ ከግልጽነት፣ ከትክክለኛነት፣ ከተመጣጣኝነትና ከተገቢነት አንጻር ችግሮች እንዳሉ ከትንተናው ውጤት ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡ ከአደረጃጀት አንጻርም፣ የተካተቱ ሰዋስዋዊ ይዘቶ ከተከታታይነት፣ ከተለጣጣቂነት አንፃር ችግሮች ያሉ መሆኑ፣ከዝርዝር ወደ አጠቃላይ እና ከአጠቃላይ ወደ ዝርዝር አደረጃጀቶች ተመጣጣኝ ሆነው ያለመቅረብ /በሰባተኛ ክፍል መማሪያ መጽሀፍ ከአጠቃላይ ወደ ዝርዝር አደረጃጀት ስልት በስፋት ሲገኝ፣ ከዝርዝር ወደ አጠቃላይ አደረጃጀት ስልት የተዘጋጁ ስድስት ይዘቶች ብቻ ናቸው፡፡ በስምንተኛ ክፍል ደግሞ ከዝርዝር ወደ አጠቃላይ አደረጃጀት ስልትበስፋት ሲገኝ ከአተቃላይ ወደ ዝርዝር የተደራጁ ሁለት ይዘቶች ብቻ/ ችግሮች እንዳሉ ለማየት ተሞክሯል፡፡ በመጨረሻመም በዚህ ጥናት ውስጥ በሰዋስ ይዘቶች አደረጃጀት ላይ የታዩ ድክመቶችን ለማሻሻል ያስችላሉ ተብሎ የታመነባቸው የመፍትሄ ሀሳቦች ተጠቁመዋል፡፡ የመጀመሪያው በጥናትና ምርምር ውጤቶች የተጠቆሙ አስተያየቶችን ወስዶ በዝግጅት ወቅት ተግባር ላይ ማዋል፣ ሌላው መማሪያ መጻህፍት ሲዘጋጁ በተቻለ መጠን የአቀራረብና የአደጃጀት መርሆዎችን ተከትለው ቢዘጋጁ የሚሉት ናቸው፡፡
  • Item
    የግለመር የመማር ዘዴ አማርኛ ቋንቋን አንብቦ ከመረዳት ችሎታ ጋር ያለው ተዛምዶ መፈተሽ፤ በሀዲያ ዞን በምዕራብ ባዳዋቾ ወረዳ ጃርሶ ኦንጆጆ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የ9ኛ ክፍል ተማሪዎች ተተኳሪነት
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2024-08) አበበ ታሪኩ; ግርማ መንግስቱ ዶ/ር
    ይህ ጥናት ዋና ተግባር በአማርኛ ቋንቋ ትምህርት የግለ መር መማር ዘዴ አንብቦ ከመረዳት ችሎታ ጋር ያለውን ተዛምዶ መፈተሽ ሲሆን ፣ ይህንን አላማ ከዳር ለማድረስ ጥናቱ ተዛምዷዊ የምርምር ንድፍን ተከትሏል ። በሀዲያ ዞን በምዕራብ በደዋቾ ወረዳ ጆርሶ ኦንጆጆ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በአመቺ የናሙና አመራረጥ ዘዴ ተመርጧል ። የጥናቱ ተሳታፊዎች የጆርሶ ኦንጆጆ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በ2015 ዓ.ም የሚማሩ በአመቺ ናሙና የተመረጡ የ9ኛ ክፍል ተማሪዎች ሲሆኑ፣ጥናቱ የተከተለው ቅንጅታዊ የምርምር ዘዴን ነው በፅሁፍ መጠይቅ እና በአንብቦ መረዳት ፈተና ለጥናቱ አሰፈላጊ የሆኑ ግብአቶች ተሰብሰበውና ተጠናቅረው በመጠናዊ የምርምር ዘዴ በሆነው በድብልቅ የአተናተን ስልት ተተንትኖ ቀርቧል። ትንተናውን ለማካሄድ SPSS Software ተግባራዊ ሆኖዋል፡፡ የጥናቱ ውጤት ተማሪዎች ንዑሳን የግለ መር መማር ዘዴዎችን ግብ ማስቀመጥ፣የመማር ፍላጎትና የመማር ዘዴ እንደሚጠቀሙ አመልክቷዋል ። በግለመር መማር ዘዴና አንብቦ በመረዳት ችሎታ መካከል አዎንታዊ የሆነ ግኑኝነት እንዳለም የጥናቱ ውጤት አማልክቷል ። ሌላው ግለ መር የመማር ዘዴዎች አንብቦ የመረዳት ችሎታን የማሳደግ ድርሻቸው ከፍተኛ እንደሆነም የጥናቱ ውጤት ያመለክታል። በመጨረሻም በዚህ ጥናት ባልተጨማሩ በሌሎች የግለመር የመማር ዘዴ ንዑሳን ክፍሎች የተለያዩ ጥናት ቢያካሄዱ የተማሪዎችን የአንብቦ መረዳት ችሎታ ለማሳደግ ያለው አስተዋጾ የተሻለ ውጤት እንደሚያመጡ የጥናቱ ውጤት አሳይቷል፡፡
  • Item
    መስተጋብራዊ የማስተማሪያ ዘዴ መስማት በተሳናቸው ተማሪዎች የመጻፍ ክሂል ችሎታና የመማር ፍላጎት ላይ ያለው ተጽዕኖ (በሰባተኛ ክፍል ላይ የተካሄደ ሙከራዊ ጥናት)
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2024-05) እታገኝ ገደፋው; ዶ/ር ጌታቸው እንዳላማው
    የዚህጥናትዋናኛዓላማ መስተጋብራዊ የማስተማሪያዘዴመስማት የተሳናቸው ተማሪዎችንየመጻፍክሂል ችሎታና የመማር ፍላጎት ከማሻሻልአንጻርያለውንተጽዕኖመመርመርነው፡፡ጥናቱ በአንድ የሙከራ ቡድን ንድፍ(Single Group Experimental Design) ላይ በመመስረት የተከናወነ ሲሆንይህየምርምርንድፍምየጥናት ናሙናን በመምረጥ ሂደት የተጠኚዎች ቁጥር ለሁለት ቡድን ማለትም ለጥብቅ (Control) ለሙከራ (Exprmental) ሳይበቃ ሲቀር የሚመረጥ ነው፡፡ጥናቱየተካሄደው በአዲስ አበባ መስተዳድር ስር ከሚገኙ መስማት የተሳናቸው ተማሪዎች ትምህርት ቤቶች መካከል በአልፋ መስማት የተሳናቸው ተማሪዎች የመጀመሪያ ደረጃ ልዩ ትምህርት ቤት ሲሆን በትምህርትቤቱከሚገኙ የክፍል ደረጃዎች መካከል ለጥናቱ የተመረጠው ክፍል ሰባተኛ ነው፡፡ ትምህርት ቤቱንና የክፍል ደረጃውን በመምረጥ ረገድ አላማ ተኮር ናሙና (purposive Sampling)ተግባራዊ ተደርጓል፡፡ በጥናቱ ተሳታፊ የሆኑት ተማሪዎች በጠቅላይ ናሙና(Comprehensive Sampling)የተመረጡ ሲሆን በዚህም በክፍል ደረጃው የሚማሩ ሁሉም ተማሪዎች (ሰባቱም) በጥናቱ ተካተዋል፡፡ እነዚህ ተማሪዎች በቀጥታ በጥናቱ እንዲሳተፉ የተደረገበት ዋናው ምክንያት ቁጥራቸው ውስንና ከተጠቀሰው በላይ ባለመሆኑ ነው፡፡ለጥናቱ በመረጃመስብሰቢያዘዴነት ተግባር ላይ የዋሉት ፈተና፣የጽሑፍመጠይቅናየተማሪዎች የቡድን ተኮር ውይይት ናቸው፡፡ ፈተናውቅድመናድህረ ትምህርት ፈተና ሲሆን ዋነኛ አላማውም ተጠኚ ተማሪዎችበመስተጋብራዊ የማስተማሪያ ዘዴ ከመማራቸው በፊትና በኋላ ያላቸውየመጻፍክሂልችሎታ ጉልህ ልዩነት ማሳየት አለማሳየቱን ለማወቅ ነው፡፡ የጽሁፍ መጠይቁም በቅድመና ድህረ ትምህርቱ ትግበራ ወቅት የሚሞላ ሲሆን አላማው ተጠኚ ተማሪዎች በመስተጋብራዊ የማስተማሪያ ዘዴ ከመማራቸው በፊትና በኋላ የነበራቸው የመጻፍ ክሂል ትምህርት የመማር ፍላጎት ምን ያህል ጉልህ ልዩነት እንዳሳየ ማረጋገጥ ነው፡፡ ሌላኛው የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴ ሆኖ ያገለገለው የቡድን ተኮር ውይይት ሲሆን አላማው ደግሞ በፈተናና በጽሁፍ መጠይቅ ለተሰበሰቡት መረጃዎች ማጠናከሪያ ሀሳብ ማስገኘት ነው፡፡በዚህም መሰረት የመጻፍ ክሂል ፈተናውና የጽሁፍ መጠይቁ በቅድመና ድህረ ትምህርት ትግበራው ላይ ለተጠኚዎች ቀርበው መረጃ የተሰበሰበባቸው ሲሆን የተገኘው ውጤትም በጥንድ ናሙና ቲ- ቴስት (Paird sample t-test) መጠናዊየመረጃ መተንተኛ ስልት ተሰልቶ ( P< 0.05)የሆነ የጉልህነት መለያ ውጤት ተገኝቷል፡፡ በአንጻሩ በቡድን ተኮር ውይይቱ የተሰበሰበው መረጃም በአይነታዊ የመረጃ መተንተኛ ዘዴ ተተንትኖ በፈተናውና በጽሁፍ መጠይቁ የተገኘውን የሚደግፍ ውጤት አስገኝቷል፡፡በአጠቃላይ በሶስቱ የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴዎች ተሰብስበው ከተተነተኑት መረጃዎች የተገኘው ውጤት የሚያመለክተው መስተጋብራዊ የማስተማሪያ ዘዴ መስማት በተሳናቸው ተማሪዎች የመጻፍ ክሂል ችሎታና የመማር ፍላጎት ላይ የሚያሳድረው ተጽእኖ መኖሩንና ተጽዕኖውም አዎንታዊ መሆኑን ነው፡፡
  • Item
    የ9ኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መምህራን ጽሕፈት ለማስተማር የሚጠቀሟቸው የማስተማር ዘዴዎች ንጽጽር በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአየር ጤና እና በክሩዝ 2ኛ ደረረጃ ት/ቤቶች
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2024-09) እጅጋየሁ ተሾመ; ዶ/ር ጌታቸው አዱኛ
    በመምህራን ውጤት መካከል ጉልህ ልዩነት መኖሩን እንረዳለን፡፡ በዚህም አማካኝ ስሌት ሆነ የቴ-ስሌት ውጤት በመንግስት ት/ቤት ከሚያስተምሩ መምህራን ይልቅ በግል ት/ቤት የሚያስተምሩ መምህራን ውጤት በልጦ በመገኘቱ የግል ት/ቤት መምህራን የተሻለ አተገባበር ያላቸው ሆነው ተገኝተዋል፡፡ ለዚህም ምክንያቱ የመምህራን እቅድ አዘገጃጀት ለተማሪዎች የግል መመሪያ መስጠት፤ አፋጣኝ ምጋቤ ምላሽ አሰጣጥ፤ ማስተማሪያ ዘዴ ወዘተ..መሆኑን መረዳት ተችሏል፡፡ ከተለዩት ችግሮች በመነሳት መመህራን ጽህፈት ለማስተማር ዘዴ ከማስተማር ሲያቅዱ በግል ማስተማሪያዎች እንደሚጠቀሙባቸው፤ የጽህፈት ችሎታን የሚያግዙ የተለያዩ መልመጃዎችን መስጠት እንደሚገባ ወዘተ.. የሚሉ አስተያየቶችም በጥናቱየዚህ ጥናት ዋና አላማ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሚገኙ የግልና የመንግስት ት/ቤቶች የ9ኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ክፍለ ጊዜ በተማሪዎች የጽህፈት ትምህርት ወቅት የትኞቹ መምህራን የማስተማር ዘዴ ጥሩ አተገባበር እንዳላቸው በመፈተሸና በመለየት ንጽጽራዊ ጥናት ማድረግ ነው፡፡ በዚህ ጥናት የተመረጡት በ 2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደደር በመንግስትና በግል ት/ቤት የ9ኛ ክፍል አማርኛ ቋንቋ የሚያስተምተሩ መምህራን ናቸው፡፡ በመስተዳደሩ ከሚገኙት መምህራን መካከል በዚህ ጥናት አንድ የመንግስት እና አንድ የግል ት/ቤት ተመርጠዋል፡፡ ጥናቱ በሚካሄድባቸው ት/ቤቶች በተመረጠው የክፍል ደረጃ ከሚያስተምሩ መምህራን ከመንግስት ትምህርት ቤቶች አራት ከግል ት/ቤት አራት በድምሩ ስምንት መምህራን እንዲሁም ከግል ት/ቤቶች 40 ከመንግስት ት/ቤቶች 40 በድምሩ ሰማኒያ ተማሪዎች በክፍል ምልከታ እና የጽሁፍ መጠይቅ በመረጃ ሰጪነት ተካተዋል፡፡ ጥናቱ የተከተለው የአጠናን ስልት አይነታዊና እና መጠናዊ የምርምር ዘዴን በመጠቀም በገለጻ ስልት ትንታኔ በመስጠት ነው፡፡ የክፍል ውስጥ ምልከታ እና የጽሁፍ መጠይቅ መረጃ የተሰበሰበባቸው መሳሪያዎች ናቸው፡፡ በዚህ መሰረት ከክፍል ምልከታ እና ከተማሪዎች የጽሁፍ መጠይቅ የተገኘው ውጤት በባለሙያ በመታገዝ በSPSS ተሰርቷል፡፡ በመሆኑም ምልከታ የተገኘ ውጤት በመንግስት ት/ቤት 3.797 ፤ በግል ት/ቤት 4.395 አማካኝ ውጤት ያለ ያስመዘገቡ የተማሪዎች የግምገማ ውጤት ደግሞ የመንግስት ት/ቤቶ 3.809፤ የግል ት/ቤት 4.25 አማካኝ ውጤት አስመዝግበዋል፡፡ በመምህራን መካከል ጽሕፈት በማስተማር ዘዴ የጎላ ልዩነት መኖርና አለመኖሩን ለማረጋገጥ በተደረገው ስሌት በክፍል ውስጥ ምልከታ የቴ- ስሌት ዋጋ 3-435 ሲሆን የቴ- የቴ- ጣሪያ ዋጋ ደግሞ 2-542 ነው፡፡ የተማሪዎች ግምገማ የቴ-ስሌት ዋጋ 4-320 ሲሆን የቴ-ጣቲያ ዋጋ ደግሞ 2-352 ነው፡፡ ከተገኘው ውጤት መረጃ በመነሳት የቲ - ስሌት ዋጋ ከቲ ጣሪያ ከበለጠ አስተያየት ተሰጥቶባቸዋል፡፡
  • Item
    የአማርኛ ቋንቋ መምህራን የመፃፍ ክሂል ማስተማሪያ ዘዴዎች አተገባበር /በጋሞ ዞን በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ በ9ኛ እና በ10ኛ ክፍል/
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2024-01) ዘሪሁን አሰፋ; ግርማ ገብሬ ዶ/ር
    የዚህ ጥናት ዋና ዓላማ በጋሞ ዞን በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የዘጠነኛ እና የአስረኛ ክፍሎች የአማርኛ ቋንቋ መምህራን የመፃፍ ክሂል ማስተማሪያ ዘዴቾን አተገባበርን የሚመለከት ነው፡፡ ይህን ዓላማ ከግብ ለማድረስ የቋንቋ ምሁራን ያቀረቧቸውን ንድፈ ሀሳቦች መሰረት በመድረግ በጥናቱ የተሳተፉት የአማርኛ ቋንቋ መምህራን የመጻፍ ክሂል ማስተማሪያ ዘዴዎች አተገባበር እንዲከወን ተደርጓል፡፡ ጥናቱን ከዳር ለማድረስ ምልከታ ጥቅም ላይ የዋለ ሲሆን በተቸማሪ የጽሁፍ መጠይቆችን በመምህራንና በተማሪዎች በመስሞላት መምህራን ጽህፈትን ስለሚያስተምሩበት የማስተማሪያ ዘዴ የሚጠቅሙ መረጃዎች ተሰብስበዋል፡፡ መረጃዎቹ የአይነታዊ ምርምር ዘዴን በመጠቀም በገላጭ ስልት ተተንትነዋ፡፡ ከጥናቱ የተገኘው ውጤት እንደሚያመለክተው መምህራን ተማሪዎችን በተግባራዊ ሂደት እንዲማሩ ከማመቻቸት ይልቅ በገለጻ የሚያስተምሩ መሆናቸውን መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ በክፍል ውስጥ ተግባራዊ የሚደረገው የማስተማሪያ ዘዴ የጽህፈት ተግባቦትን የሚያዳብር እና ተማሪዎችን የሚያሳትፍ አይደለም፡፡ ተማሪዎች የተለያዩ ለጽህፈት ክሂል ማዳበር የሚረዱ ሂደቶችን አውቀው እየተገበሩ እንዲሻሻሉ የሚደረግ ጥረት ደካማ ነው፡፡ ተማሪዎች እርስ በርስ እንዲመማሩና እንዲተራረሙ የሚተገበረው ተግባር ውስንነት አለበት፡፡ በአባዛኛው መምህራን ትኩረት ሰጥተው የሚተገብሩት ተማሪው በተሰጠው ርዕስ ላይ ጽፎ ባቀረበው ውጤት ላይ ነው፡፡ ለችግሩ መኖር በዋናነት የተጠቀሰው መንስኤ መምህራን ለጽህፈት ትምህርት አቀራረብ ያላቸው ግንዛቤ አነስተኛ በመሆኑ ነው፡፡ በአጠቃላይ ለችሮቹ መፍተሔ ሊሆን ይችላል ተብሎ የሚገመተው መምህራን ከአዳዲስ የማስተማሪያ ዘዴዎች ጋር እንዲተዋወቁ ስልጠና መስጠት ተጦቁሟል፡፡
  • Item
    ሂደት ተኮር አቀራረብ የተማሪዎችንት የመጻፍ ችሎታ እና ተነሳሽነት ለማሻሻል ያለው አሰተዋጽኦ (በጉራጌ ዞን በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በጅማ ወለኔ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በ9ኛ ክፍል ተተኳሪነት)
    (አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2024-07) የሰራሽ አደራው; ግርማ ገብሬ (ዶ/ር)
    ይህ ጥናታዊ ጽሁፋ ዋነኛ ዓላማ አድርጎ የተነሳው የሂደት ተኮር የቋንቋ ማስተማር ዘዴ የተማሪዎችየመጻፍ ክሂል ችሎታ እና ተነሳሽነት ከማሻሻል አንጻር ያለውን አስተዋጽኦ ለመፈተሽ ነው፡፡ ጥናቱም ከፊል ሙከራዊ ሲሆን፣ የተካሄደውም በደቡብ ክልል በጉራጌ ዞን በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በሚገኘው በጅማ ወለኔ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ነው፡፡ በትምህርት ቤቱ ከሚገኙ ተማሪዎች መካከል የ9ኛክፍል ተማሪዎች በአመቺ የናሙና ስልት ከተመረጡ በኋላ፣ በተራ ዕጣ የናሙና አመራረጥ ስልት በአንድ መምህር የሚማሩ ሁለት ምድብተማሪዎች ተለይተው በቅድመ ፈተናው ሂደት ተሳትፈዋል፡፡ ከሁለቱ ምድቦች መካከል በቅድመ የመጻፍ ክሂል ፈተና ተቀራራቢ አማካይ ውጤቶች ያስመዘገቡ ሁለት ምድቦች ከተለዩ በኋላ በተራ የዕጣ ናሙና ስልት አንዱ የሙከራ ሌላኛው የቁጥጥር ቡድን ሆኖ በጥናቱ ውስጥ እንዲሳተፍ ተደርጓል፡፡ በመረጃ መስብሰቢያ ዘዴነት ፈተና እና የጽሑፍ መጠይቅ ሥራ ላይ ውለዋል፡፡ ፈተናው፣ ቅድመ እና ድኅረ ፈተናን ያካተተ ነው፡፡ ቅድመ ፈተናው የተሰጠበት ዓላማ ተማሪዎች ከሙከራ ጥናቱ በፊት ያላቸውን የመጻፍ ክሂል ውጤት ተቀራራቢ መሆን አለመሆኑን ለመፈተሽ ሲባል ነው፡፡ የድኅረ ፈተናው ዓላማ ደግሞ የሙከራ እና የቁጥጥር ቡድን ሆነው የተመረጡት ተማሪዎች በተለያዩ የማስተማሪያ ዘዴዎች የመጻፍ ክሂልን ከተማሩ በኋላ በመካከላቸው ጉልህ ልዩነት መኖር አለመኖሩን ለመፈተሽ ነው፡፡ በሌላ በኩል የጽሑፍ መጠይቅ የተማሪዎቹን የመጻፍ ተነሳሽነት ለመለካት የቀረበ ነው፡፡ ተተኳሪ የሆኑት ተማሪዎች ከመጻፍ ልምምዱ በፊት (ቅድመ ጽሑፍ መጠይቅ) እና በኋላ (ድኅረ የጽሑፍ መጠይቅ) እንዲሞሉ ተደርጓል፡፡ በቅድመ ፈተና እና በቅድመ የጽሑፍ መጠይቅ የተገኙ ውጤቶች በዳግም ናሙና ቲ-ቴስት ትንተና ዘዴ እንዲሁም በድኅረ ፈተና እና በድኅረ የጽሑፍ መጠይቅ የተገኙ ውጤቶች በባዓድ ናሙና ቲ-ቴስት ትንተና ዘዴ እንዲሰሉ ተደርጓል፡፡ የተገኙት ውጤቶች እንደሚያመለክቱት በቅድመ ፈተና እና በቅድመ የጽሑፍ መጠይቅ ተመጣጣኝ አማካይ ውጤቶች የተመዘገበባቸው ቡድኖች፣ በድኅረ ፈተና ይዘት፣ አደረጃጀት፣ ቃላት፣የቋንቋ አጠቃቀም እና ሥርዓተ አጻጻፍ እና በድኅረ የጽሑፍ መጠይቅ ተነሳሽነት የሙከራ ቡድኑ ተማሪዎች ከቁጥጥር ቡድኑ ተማሪዎች ጉልህ የሆነ ልዩነት አሳይተዋል።ይህም ውጤት የሂደት ተኮር የቋንቋ ማስተማር ዘዴ የተማሪዎችን የመጻፍ ክሂል ችሎታ እና ተነሳሽነት ከማሻሻል አኳያ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው ሊጠቁም ችሏል፡፡ ከመጻፍ ክሂልችሎታ እና ተነሳሽኘት አንጻር የተገኙት ውጤቶች ላይ በመመስረት ማብራሪያ እንዲሰጥባቸው ከተደረገ በኋላ፣ የሂደታዊ ዘዴ የመፃፍ ትምህርት አቀራረብ የተማሪዎችን የመፃፍ ክሂል ለማዳበር ጥሩ አስተዋፅዖ ያለው መሆኑ በጥናቱ ተረጋግጧል፡፡ መምህራን ጥሩ ግንዛቤ ኖሯቸው በክፍል ውስጥ በተገቢው ሁኔታ መተግበር እንዲችሉ የሚያደርጋቸው በቂ ስልጠና ሊሰጣቸው ይገባል፡፡ የመፍትሄ ሀሳቦች እና የጥናት ጥቆማዎች እንዲቀርቡ ተደርጓል።