Amharic Language, Literature and Folklore
Permanent URI for this collection
Browse
Recent Submissions
Item የወሊይታ ብሔረሰብ ቁሳዊ ባህሌ ጥናት በባህሊዊ የቤት አሰራር ተተኳሪነት.(Addis Ababa University, 2025-04-20) ደነቁ አበረ; ዓለሙ ካሣዬይህ ጥናት ‛የወሊይታ ብሔረሰብ ቁሳዊ ባህሌ ጥናት በባህሊዊ የቤት አሰራር ተተኳሪነት“ በሚሌ ርዕስ ተካሂዶሌ፡፡ ዏቢይ ዓሊማው የወሊይታን ብሔረሰብ ባህሊዊ የቤት አሰራር ሂዯት መተንተን ነው፡፡ በብሔረሰቡ በዓይነትና በአገሌግልት በርካታ የቤት ዓይነቶች ቢኖሩም በዚህ ጥናት ሇሰዎች መኖሪያነት የሚያገሇግለ የባህሊዊ ቤቶች አሠራር ተተኳሪ ተዯርገዋሌ ፡፡ ጥናቱ ዓይነታዊ የምርምር ዘዳን የተከተሇ ሲሆን፣ መረጃዎችም በወሊይታ ዞን ከሚገኙ አምስት ወረዲዎች ውስጥ ከአሥር ቀበላዎች በዓሊማ ተኮር ናሙና እና በጠቋሚ ናሙና ከተመረጡ ሰባ መረጃ አቀባዮች ተሰብስበዋሌ፡፡ የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዳዎችም ምሌከታ፣ ቃሇመጠይቅና የቡዴን ውይይት ሲሆኑ፣የተገኙት መረጃዎችም በማህበራዊ ትምህርት፣ በመዋቅራዊ ተግባራዊነት፣በሥነ ትእምርትና በማህበራዊ ግንባታ ንዴፇ ሃሳቦችሃሳቦች ታግዘው በገሊጭ መንገዴ ተተንትነዋሌ፡፡ የጥናቱ ውጤት እንዯሚያሳየው የወሊይታ ባህሊዊ ቤቶች ዙፊ፣ሜሹዋ፣ ጉሊንታናቡራሪያ በመባሌ በአራት አይነት ይከፇሊለ፡፡ ቤቶቹ ከውጭ ሲታዩ ተመሳሳይነት የሚታይባቸው ቢሆኑም ውስጣዊ አሰራራቸው የተሇያየ ነው፡፡ በተሇይ ‘ጉሊንታ’ የተሰኘው ቤት አሰራሩ የዘጠኙን ፕሊኔቶች አቀማመጥ መከተለ ሌዩ ያዯርገዋሌ፡፡ የቤት አሰራር ሂዯት ከቦታና ከግንባታ ቀናት መረጣ (የጨረቃን ዐዯት ጨምሮ) ጀምሮ በብሔረሰቡ ሽማግላዎች ፇቃዴና ቡራኬ የሚከናወን፣ ከፌተኛ ማኅበራዊ ተሳትፍ የሚታይበትና በሥርዓት የሚመራ ነው፡፡ የቤቱ ክብ ቅርጽ ‘ሙለነትን’፣ ሇጌጥነት የሚያገሇግለት ቀሇማት ዯግሞ የብሔረሰቡን ማንነትን የሚወክለ ሲሆን፣ በተሇይ ዋናው ምሰሶ ከማኅበራዊ ክብር፣ ከመንጻት፣ከእምነትና ከሥርዓተ ጾታ ጋር የተያያዙ ጥሌቅ ትርጉሞችን ይዟሌ፡፡ በተጨማሪም የግንባታው ሂዯት በባህሊዊ ዘፇኖች፣ በምሳላያዊ ንግግሮችና በምርቃቶች የታጀበ ነው፡፡ በብሔረሰቡ ቤት በሚሰራበት ወቅት የብሔረሰቡ ተጠሪዎች፣አባቶች፣እናቶች፣ወጣቶች፣የቤተሰቡ አባሊት፣ጎረቤቶች፣ ዘመድችና የአካባቢው ህዝብ ቀዯም ሲሌ በተሰጣቸው የሥራ ዴርሻ መሰረት የተሇያዩ ስራዎችን በመከወን የቤቱን ባሇቤቶች ያግዛለ፡፡ ባህሊዊ ቤት በሚሰራበት ወቅት የምሰሶውን ጫፌ ሇሚጠርቡ ባሇሙያዎች፤የበር ጉበንና መግቢያውን ሇሚያስውቡ ግዴግዲ ሇሚሰሩ፣ጣሪያ ሇሚሰሩ ባሇሙያዎች የተሇያዩ ምግቦች የሚቀርቡ ሲሆን ይህም ግዴግዲ ሲሰሩ ከአዯንጓሬና ከበቆል ንፌሮ ይዘጋጃሌ፣ጣሪያ የሚሰሩ ሰዎች በሙያው እውቀት (ሌምዴ) የገበዩ ሰዎች ስሇሆኑ ባጭራ፣ፊጫታ የሚባለ የተሇዩ በወሊይታ ባህሌ መሰረት የክብር ምግቦች ይዘጋጅሊቸዋሌ፡፡ ሇምግቡ ማቅረቢያ አንዴ ወጥ የሆነ እርጥብ ኮባ በተቀመጡት ሰዎች ፉት ሇፉት ወሇለ ሊይ ይነጠፊሌ፤ ምግቡም የሚቀርበው በዚሁ ኮባ ሊይ ሲሆን የኮባው እርጥብ መሆን ትርጓሜም ነገር ሁለ መሌካም ይሁን፣ሁለም እርጥብ ይሁን እንዯ ማሇት ነው፡፡ የቤት አሰራር እውቀት ተስተሊሌፍን በተመሇከተ አባቶች ሌጆችን አስከትሇው በመሄዴ ቀሇሌ ያለ ስራዎችን እንዱሰሩ በማዴረግና በማሳየት እውቀቱን እንዱሇምደ ያዯርጓቸዋሌ፡፡ ምንም እንኳ በአሁኑ ወቅት ባህሊዊ የሳር ቤቶች ቁጥር እየቀነሰ ቢመጣም፣ በምትካቸው የሚሰሩ ዘመናዊ ቤቶች የዴሮዎቹን ውስጣዊ አቀማመጥና አንዲንዴ ቁሶች ይዘው ተገኝተዋሌ ፡፡ በተጨማሪም ቆርቆሮ ቤቶቹ ሳር ቤቶቹ ውስጥ ያለ ቁሶችን ይዘው የቀጠለ ሲሆን ሳር ቤቶቹ ባህሊዊውን አሰራር ተከትሇው የተሰሩ ቢሆንም ቆርቆሮ ቤቶች ውስጥ የሚገኙ ቁሶችን በመያዛቸው ሳር ቤቶቹ ሊይ የቀጠሇውንና የተሇወጠውን ከጥናቱ መረዲት ተችሎሌ፡፡ በዚህ መሰረት የወሊይታ ባህሊዊ የቤት አሰራር ጥበብ ከመኖሪያነት ባሇፇ ከሥነ ፇሇክ (ከፕሊኔቶችና ከጨረቃ)፣ ከማኅበራዊ አዯረጃጀትና ከፌሌስፌና ጋር ጥብቅ ቁርኝት ያሇው መሆኑን ጥናቱ አሳይቷሌ ፡፡ በመሆኑም ይህ ከሥነ ፇሇክ ጋር ያሇው መስተጋብር በላልች ተመራማሪዎችና ተቋማት ሰፉ ጥናት እንዱዯረግበት ይመከራሌ ፡፡Item የማዳመጥ ክሂልን ለማስተማር የተዘጋጁ የ 8ኛ ክፍል የአማር ኛ ቋንቋ ትምህርት ምንባቦችና መልመጃዎች አቀራረብ ፍተሻ(Addis Ababa University, 2024-04-01) ነጻነት ናኔቻ; ሙሉሠው አስራቴይህ ጥና ት ይዞ ት የ ተ ነ ሳ ው አ ቢይ አ ላ ማ የ ማዳመጥ ክ ሂ ል ን ለ ማዳ በ ር የ ተ ዘ ጋ ጁ የ 8ኛ ክ ፍል የ አ ማር ኛ ቋ ን ቋ ትምህ ር ት ምን ባ ቦ ችና መል መጃ ዎች አ ቀ ራረ ብን መፈተሸ ነ ው፡ ፡ ጥና ቱን ከ ግብ ለ ማድረ ስ አ ጥኚዋ በ ዋነ ኛ ነ ት አ ይነ ታዊ ምር ምር የ ተጠቀመች ሲሆን በ ደ ጋ ፊ ነ ት ደ ግሞ መጠና ዊ ምር ምር ን ተጠቅማለ ች፡ ፡ የ መረ ጃ መሰ ብሰ ቢያ መሳ ሪ ያ ዎች የ ሰ ነ ድ ፍተሻ ፣ በ መምህ ራን የ ተሞሉ የ ጽሁፍ መጠይቆ ች እ ና የ ክ ፍል ምል ከ ታ ና ቸው፡ ፡ ከ መረ ጃ ምን ጮች የ ተገ ኘ ው መረ ጃ በ አ ግባ ቡ ተደ ራጅተው ትን ተና ተደ ር ጎ ባ ቸዋል ፡ ፡ ለ ጥና ቱ አ ላ ማ ተኮ ር የ ና ሙና አ መራረ ጥ ዘ ዴን በ መከ ተል የ ስ ምን ተኛ ክ ፍል የ አ ማር ኛ ቋ ን ቋ መማሪ ያ ና ማስ ተማሪ ያ መጽሐፍት የ ተመረ ጡ ሲሆን ፤ በ ጠቅ ላ ይ የ ና ሙና አ መራረ ጥ 12 መምህ ራን የ ጽሁፍ መጠይቅ እ ን ዲሞሉ ተደ ር ጓ ል ፡ ፡ ፤ እ ን ዲሁም ስ ድስ ት መምህ ራን ክ ፍል ውስ ጥ ሲያ ስ ተምሩ የ ክ ፍል ምል ከ ታ ተደ ር ጓ ል ፡ ፡ ከ መረ ጃ ዎቹ የ ተገ ኙት ውጤቶች የ ሚያ መለ ክ ቱት ማዳመጥን ለ ማስ ተማር የ ተ ዘ ጋ ጁት ምን ባ ቦ ች ከ ተማሪ ዎች የ ዕ ለ ት ገ ጠመኝ ጋ ር ያ ላ ቸው ግ ን ኙነ ት አ ነ ስ ተኛ መሆኑ እ ን ዲሁም በ ቅድመ ማዳመጥ በ ማዳመጥ ጊ ዜና በ ድህ ረ ማዳመጥ ጊ ዜ የ ሚቀ ር ቡ ጥያ ቄዎች የ ቀ ረ ቡበ ትን አ ላ ማ ለ ማሳ ካ ት የ ሚያ ስ ችሉ ሆነ ው አ ለ መቅ ረ ባ ቸውን ፣ ለ ማስ ተማሪ ያ ነ ት የ ቀ ረ ቡት ምን ባ ቦ ች አ ስ ፈላ ጊ የ ማስ ተማሪ ያ መሳ ሪ ያ አ ለ ማካ ተታቸውን ፣ ስ ለ ዚህ ም እ ነ ዚህ ን የ ጥና ት ውጤቶችን መሰ ረ ት በ ማድረ ግ ለ ወደ ፊቱ አ ሻ ሽ ሎ ለ ማቅ ረ ብ የ ሚያ ስ ችሉ አ ስ ተያ የ ቶች ቀ ር በ ዋል ፡ ፡Item ፍክልራዊ ፊይዲ በተመረጡ 3 ትውፉታዊ ተውኔቶች ማሳያነት.(Addis Ababa University, 2017-11-10) ንጉሥ ባይሌ; የወንዴወሰን አውሊቸውይህ ጥናት “ምስጢሩ” (2011 ዒ.ም)፣ “ተጠየቅ” (2013 ዒ.ም) እና ሸምጋይ” (2015 ዒ.ም) በተሰኙ ትውፉታዊ ተውኔቶች ውስጥ የሚገኙ የፍክልራዊ ጉዲዮችን በመሇዬት ፊይዲቸውን የመተንተን አሊማ ይዝ የተሰራ ነው። ይህንንም ሇማሳካት ተውኔቶቹን በቀዲማይ ምንጭነት፤ ከተሇያዩ ቤተ-መጽሀፌት፣ የምርምር ተቋማት እና ዴረ-ገጾች ሊይ ተገኙትን ንዯፇ-ሀሳብ እና ጽነሰ-ሀሳሳቦች የያዘ ጽሁፍችን በካሌዒይ ምንጭነት ተጠቅሟሌ፡፡እነዙህን መረጃዎችንም የሰነዴ ትንተና (Textual analysis) የመረጃ አተናተን ዳን ጥቅም ሊይ በማዋሌጥናቱን አካሂዶሌ፡፡ ትንታነው ሲዯረግም ተግባራዊ ንዴፇ ሀሳብን (Functional theory) ማሳያ በማዴረግ ነው፡፡ በትንተናው መሰረትም ማዎቅ ተችሎሌ። በ“ሸምጋይ” ተውኔት ወስጥ በፉውዲለ እና በሰራተኛው መዯብ መካከሌ የሚታዩ የአኗኗር እሴቶችን እና ሌማድችን መመሌከት የሚቻሌ ሲሆን “ተጠየቅ” በተሰኘው ተውኔትም ባህሊዊ የእርቅ ሥነ-ሥርዒት የተውኔቱ ማዕከሊዊ ሀሳብ ሆኖ ቀርቧሌ፡፡ ከዙህ በተጨማሪም “ምስጢሩ” በተሰኘው ተውኔት ዯግሞ በተውኔቱ ውስጥ የተጠቀሰው ወንጀሇኛን ሇመሇየት የሚጠቀምበት “አውጫጭኝ” ተብል የሚታወቀው ባህሊዊ የወንጀሇኛ ምርመራ ዳ ሇተውኔቱ ዋና ጭብጥነት ቀርቧሌ። በተውኔቶቹ ውስጥ የቀረቡት የተሇያዩ ባህሊዊ ሥርዒቶች፣ ሌማድች፣ እምነቶች እና አስተሳሰቦች ግሌጽ እና አዜናኝ በሆነ ኪነ-ጥበባዊ በሆነ መንገዴ በመቅረባቸው ፍክልራዊ ጉዲዩን በቀሊለ ሇመረዲት ያስችሊለ። ይህ አቀራረብም ፍክልርን መሰረት አዴርገው የሚሰሩ ተውኔቶች የአንዴን ሀገር ባህሊዊ እሴቶች፣ ታሪክና ማኅበራዊ እምነቶችን ሇማሳወቅ፣ ሇመጠበቅና ሇመጪው ትውሌዴ ሇማስተሊሇፌ የራሳቸውን ሚና እንዯሚጫወቱ በጥናቱ ሇመገንብ ተችሎሌ፡፡ ከዙህም በተጨማሪ፣ እነዙህ ተውኔቶች በተሇያዩ ማህበራዊ ጉዲዮች ሊይ አስተያየት በመስጠት፣ በትውሌድች መካከሌ ግንኙነት እንዱፇጠር፣ ማህበራዊ ግንዚቤ እንዱያዴግ እና ሇመዜናኛነት እንዯሚያገሇግለ ጥናቱ አረጋግጧሌ። ይህ ጥናት ሇቀጣይ ተመራማሪዎች በኢትዮጵያ ፍክልርና ትውፉታዊ ቴአትርን በየበሌጥ ሇማስተዋወቅ የራሱን አስተዋጽኦ ያበረክታሌ።Item በአማርኛ አጫጭር ልብ ወለዶች ውስጥ የዐይነ ስውራን ገጸባህሪያት አሳሳሌና ጭብጥ ትንተና(Addis Ababa University, 2026-01-20) ጌታቸው ሞገስ; አየሇ ፍቅሬይህ ጥናት የተካሄዯበት ዋነኛው ምክንያት በዐይነ ስውራን ገጸባህሪያት አሳሳሌ ሊይ በቂ ጥናታዊ ጽሐፎች ባሇመኖራቸው ነው። ስሇሆነም ይህ ጥናት በርፉ ያሇውን የጥናታዊ ጽሐፍ ክፍተት ሇመሙሊት ይረዲሌ። ስነ ማህበረሰባዊ ሂስ ዯግሞ በመረጃ መተንተኛ ንዴፈ ሀሳብነት አገሌግሎሌ። ጥናቱ በአምስት የአማርኛ አጫጭር ሌብ ወሇድች (“ምራኝና እንሂዴ እኔ አንተን አዜዬ ማሙዬ፤“ “የጢሞቴዎስ ሌጅ በርጠልሜዎስ፤“ “እራትና መብራት”፣ “ወይ አዱስ አበባ፤“ እና “ቦርጨቅ“) ውስጥ የዐይነ ስውራንን ገጸ-ባህሪያት ውክሌና መርምሯሌ። ጥናቱ እነዙህ ገጸባህሪያት በስነ-ጽሐፍ ውስጥ እንዳት እንዯተሳለ፣ ምን ዓይነት ማኅበራዊ ሚናዎች እንዯተሰጣቸው እና በአጠቃሊይ ዐይነሥውርነት እንዳት እንዯቀረበ ተመሌክቷሌ። የጥናቱ ግኝቶች እንዯሚያሳዩት፣ ዯራሲያኑ ዐይነ ሥውራንን ከማኅበራዊ ሚና አንጻር ሲስለ፣ በአምስቱም ገጸባህሪያት ሊይ የሚታይ አንዴ የጋራ ጅምሊ ፍረጃ (stereotype) ተገኝቷሌ፤ ይህም ሁለም ገጸባህሪያት በአንዴም ሆነ በላሊ ወቅት ከሌመና ሕይወት ጋር መያያዚቸው ነው። በአሳሳሌ ቴክኒክ ረገዴ በአንዴ በኩሌ፣ አንዲንዴ ገጸባህሪያት (እንዯ “ታሪኩ“ እና “አሮጊቷ“)፣ ምንም ዓይነት ሰብዓዊ ግዴፈት የላሊቸው፣ “ፍጹም ሰናይ“ (idealized) ተዯርገው በመቅረባቸው የተአማኒነት ክፍተት መኖሩ ተረጋግጧሌ። በላሊ በኩሌ፣ እንዯ “ሽማግላው“፣ “ውበቴ“ እና “በርጠልሜዎስ“፣ እንዯ ፍርሃት፣ ተንኮሌ፣ ሱስ፣ ጸጸትና ጥርጣሬ ያለ ጥሌቅ ሰብዓዊ ዴክመቶችን ተሊብሰው በመገኘታቸው፣ ከጅምሊ ፍረጃ የጸደና እጅግ ተአማኒነት ያሊቸው ሆነው ተስሇዋሌ። በጭብጥ ዯረጃም፣ ዯራሲያኑ ዐይነ ሥውርነትን ተጠቅመው ሁሇት ዋና ዋና ጉዲዮችን አንስተዋሌ፦ (1) ዐይነ ሥውርነት የሚያስከትሇው ማኅበራዊ ጥገኝነት፣ ብዜበዚና መገሇሌ፣ እና (2) “እውነተኛ ብርሃን“ ምንዴን ነው? በሚሇው ዘሪያ አካሊዊ እይታን ከሌቦና ማስተዋሌ ጋር የሚያነጻጽር ጥሌቅ ፍሌስፍናዊ ጥያቄ በሰፊው ተቃኝቷሌ።Item (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እና እስልምና እምነት ተከታዮች በሚከበሩ) በልደት እና መውሊድ በዓላት ላይ የሚቀርቡ የአማርኛ መዝሙርና ትንተና ::(Addis Ababa University, 2024-01-30) ሔኖክ ደሴ; መሐመድ አሊይህ ጥናት በልደት እና በመውሊድ በዓላት ላይ የተካሄደ ሲሆን ከሥነቃል ዘውጎች ውስጥ በሚገኙትን መዝሙርና መንዙማ ላይ መሠረቱን ያደረገ ነው። ጥናቱ ይዞት የተነሳው ዋና ዓለም በልደት እና መውሊድ በዓላት ላይ የሚቀርቡ መዝሙራትና መንዙማዎች ይዘትን ከሚያነሱት ሃይማኖታዊ ጉዳይ በተጨማሪ ከማኅበራዊ ፋይዳቸው እና ከተግባራቸውን አንጻር በመመርመር እና በመተንተን የጋራ እሴቶቻቸውን መለየት የሚል ነው። ለእርሰ ጉዳዩ መመረጥ እንደ አብይ ምክንያት የመዝሙርና መንዙማ የጋራ የሆኑ እሴቶች ማመላከት ላይ የተሰራ ምንም ጥናት ባለመኖሩ ክፍተት እንዳለ መረዳቴ ነው። በቢኤ እና ኤም ኤ ደረጃ በተናጠል የተሰሩ ጥቂት ሙከራዎች ከመደረጋቸው ውጪ ግጥሞች ከሚቀርቡበት ሃይማኖታዊ ገጽታ ባሻገር ምን ዐይነት ተግባራት እና የጋራ እሴቶች አላቸው የሚለውን የሚመልሱ ጥናት አለመሰራቱ ምክንያት ምን ይኾን? የሚለው የምርምር ጥያቄ ደግሞ ሐሳቤን በደንብ አጠናክሮልኛል፡፡ እንደ ፎክሎር ተማሪነቴ ይህንን ጉዳይ ሰፋ አድርጌ ብመለከት ጥናቱ ይህን ክፍተት በመሙላት በኩል ትልቅ አስተዋፆ ይኖረዋል በማለት ይህንን ጥናት ለማድረግ ተነስቻለው። የጥናቱ ዓላም ግብ ይመታ ዘንድ የምርምር ጥያቄዎቹ ምላሽ እንዲያገኙ መረጃዎችን ከቤተ መጽሐፍት፣ከበይነ መረብ እና በቃለ መጠይቅ ተሰብስበዋል። በተጨማሪነት እነዚህ መረጃዎችን ከግብ ለማድረስም በመቅረጸ ድምጽ እና በማስታወሻ ደብተር መረጃዎች ማጠናከር ተችሏል። በእዚህ መልክ የተሰበሰቡ መረጃዎች ሃይማኖታዊ ክብረ በዓል በተባለው የጽንሰ ሃሳብ ማእቀፍ ውስጥ ታይተው መዝሙርና መንዙማን ለመፈከር በሚያስችል በተግባራዊ ንድፈ ሀሰብ በመተንተን በገለጻና በትንተና ሥልት ተብራርተው ቀርበዋል። በአጠቃላይ በጥናቱ ላይ እንደታየው የልደት እና የመውሊድ በዓል የጥበብ ዕሴት መገለጫ፣ የመንፈሳዊ እሴቶች ነጸብራቅ፣ሃይማኖታዊ እና ባህላዊ ገጽታን ማሳያ መሆኑ በጥናቱ ላይ ታይቷል። የመዝሙሮቹ እና መንዙማ ግጥሞች የማኀበረሰ ማትጊያ ፣የማንነት ማጽኛና መገንብያ መሣርያ መሆናቸው የጋራ ከሚደርጋቸው ተግባራትና እሴቶች ተረጋግጧል።Item ሇኢትዮጵያ ሥነ ጽሐፍ የፍሌስፍና ድክትሬት ዱግሪ ማሟያ የቀረበ ጥናት(Addis Ababa University, 2024-03-02) በቴዎዴሮስ ገብሬ; ዮናስ አዴማሱአዲም በዖመናዊው የአማርኛ ሥነ ጽሐፍ ውስጥ የራሱን “የኪነት ሌማዴ” ሇመፍጠር የቻሇ ዯራሲ ሲሆን፣ ሚቶልጂው ከዘሁ ሌማዴ የሚመነጭ ይሆናሌ፡፡ የአዲም ሚቶች ከአንደ ሌብ ወሇዴ ወዯ ላሊው የሚዙመቱበት ጥብቅ ኪናዊ ሥርዒት አሊቸው፡፡ ይህ ሥርዒት አንዴም በትሌም ተከታታይነት፣ አንዴም በኀሌዮትና በርእዮት ተሸጋጋሪነት ሊይ የተመሠረተ ሲሆን፤ ክትትልቹና ሽግግሮቹ የሚመሩት ቋሚ በሆኑ ትእምርቶች እና ተስፋፊ ዖይቤዎች ነው፡፡ የአዲምን ሚታዊነት ጥቅሌ በሆነ እይታ በሁሇት መፈረጅ እንችሊሇን፡፡ በመጀመሪያው ፈርጅ ከባህለ በቀዲቸው አሌያም በውሰት ባመጣቸው ነባር ሚታዊ ትረካዎች ይገሇገሊሌ፡፡ በሁሇተኛው ፈርጅ በነባሩ የሚት ሌማዴ አምሳያ “ዖመናዊ” ሚትንና ሚታዊ መታገጊያን ይፈጥራሌ፡፡ ዲሩ ግን የፈጠራቸውንም ይሁን በውሰት አምጥቶ የተገሇገሇባቸውን ሚቶች በአመዙኙ በገዙ ራሱ ባህሌ አገረሰባዊ ኪኖችና ጽንሰ ሏሳቦች ሇመግራትና ሇማሰሌጠን መሞከሩ የሌብ ወሇድቹ መሇያ ባሔርይ ነው፡፡ የአዲም “ሚቶልጂ” ሲባሌ አንዴም ሌብ ወሇድቹ የተከየኑበትን ቋንቋ ሚታዊነት ሇማመሌከትም ይሆናሌ፡፡ ከዘህ ምርምር አጠቃሊይ መንፈስ የሚሰርጸው የአዲም “ሚቶልጂ” ዒቢይ አንዴምታ “ሚቶስ” ከ “ልጎስ” ጋር ያወረዯውን ዔርቅና የፈጸመውን ዲግማዊ ጋብቻ ያጠይቃሌ፡፡ አዲም ሌብ ወሇድቹን ሇመከየን ከተገሇገሇባቸው ስሌቶች መካከሌ ዒቢዩ ሚታዊ ኅሌዮ ነው፡፡ ሚታዊ ኀሌዮ በአዲም ሌማዴ ውስጥ ጽንሰ ሏሳቦችና ንዴፈ ሏሳቦች ከሌዩ ሌዩ ዱሲፕሉኖች የሚመሇመለበት፣ ከሳይንሳዊ ኀሌዮት ወዯ ኪናዊ እሴትነት የሚሸጋገሩበት ከማሔላት ተነስቶ የስንብት ቀሇማትን የዖሇቀ እጅግ ጠንካራ ስሌት ነው፡፡ አዲም ሚታዊ ኀሌዮውን የሚያዯራበት፣ የሚያፍታታበትና ሥግው የሚያዯርግበት ሌዩ ሌዩ መባያ ጉዲዮች እና/ወይንም የማስተማሰያ-የመፈከሪያ ዏውድች አለት፡፡ በዘህ ጥናት እንዯተረጋገጠው ከመባያዎቹና ከዏውድቹ መካከሌ “ሥፍራ”፣ “አካሌ” እና “ምግብ” ዏውራዎቹ ናቸው፡፡ የዘህ ጥናት ዒቢይ ዒሊማ በአዲም ሌብ ወሇድች ውስጥ ሚቶልጂን አጠቃሊይ ፍሬም በማዴረግ ሥፍራ፣ ምግብና አካሌ አንዴም ከተፈጥሮ ክስተትነት፣ አንዴም ከሳይንሳዊ ግኝትነት ወዯ ኪናዊ እሴትነት የሚሸጋገሩበትን ስሌት መተንተን ነው፡፡ በዘህ ሥር በአንዴ በኩሌ ሚታዊ ኀሌዮውን ሥግው ያዯረገባቸው ዏውራ የመባያ ጉዲዮችና የመፈከሪያ ዏውድች የአቀራረጽ ስሌትና ተጠየቅ ተመርምረዋሌ፡፡ መባያዎች ከራሳቸው ሊሇፉ ጉዲዮች መፈከሪያነት የሚያገሇግለ ትእምርቶች በመሆናቸው፣ በዘህ ጥናት ሥፍራን፣ አካሌንና ምግብን በመተርጎም ተጨማሪ ጭብጦችን ሇማዛመር ተችሎሌ፡፡ ዖመናዊው ዯራሲ፣ አዲም ረታ “ከጥንታዊው” ዒሇም በተቀዲ ተረክና የአስተሳሰብ ዖይቤ ታግዜ ሌብ ወሇድቹን ይከይን ዖንዴ በምን ዒይነት ነገረ ኪናዊ፣ ርእዮተ ዒሇማዊና ሥነ ሌቡናዊ ምክንያቶች እንዯተገፋፋ እና/ወይንም እንዯተገዯዯ ሇመመሇስ ተሞክሯሌ፡፡ ጥናቱ ከዘህ ባሇፈ ዖመናዊዎቹ ሌብ ወሇድች የፈጠሯቸውንም ይሁን በውሰት አምጥተው የተገሇገለባቸውን ሚቶች ሇመግራትና ሇማስሊት የታገባቸው ዒበይት አገረ ሰባዊ ኪኖችና ጽንሰ ሏሳቦች ምን እንዯሚመስለ የመመርመር ሚናም አሇው፡፡Item በአማርኛ ቋንቋ ትምህርት በይዘት ተኮር ዘዴ ሰዋስውን ማስተማር የሰዋስው እውቀትን ለማዳበር ያለው ፊይዳ(Addis Ababa University, 2024-01-02) አሸናፉ ደበበ; Masfiin Wadaajooየዙህ ጥናት ዋና ዓሊማ በአማርኛ ቋንቋ ትምህርት በይዘት ተኮር ዘዴ ሰዋስውን ማስተማር የሰዋስው እውቀትን ለመጨመር ያለው ፊይዲ ምን ያህሌ እንዯሆነ መፇተሸ ነው፡፡ ይህን ዓሊማ ሇመሳካት ጥናቱ ፍትነት መሰሌ ቅዴመና ዴሕረትምህርት ባሇቁጥጥር ቡዴን ንዴፍን ተከትሎሌ፡፡ ሇዙህም የቃሉቲ ሁሇተኛ ዯረጃ ትምህርት ቤትና የክፍሌ ዯረጃው (አስረኛ ክፍሌን) በአመቺ የንሞና ዘዳ፣ ሁሇት መማሪያ ክፍልችን (10B እና 10E) በቀሊሌ የእጣ ንሞና ስሌት እንዱሁም በመማሪያ ክፍልቹ የሚማሩ 95 ተማሪዎች በጠቅሊይ የንሞና ስሌት በጥናቱ ተሳታፉነት ተመርጠዋሌ፡፡ ከ95 ተማሪዎች መረጃ የተሰበሰበው በቅዴመና ዴሕረትምህርት የሰዋስው እውቀት መሇኪያ ፇተና ነው፡፡ አስተማማኝነቱን ሇመፇተሽም በዋናው ጥናት ባሌተሳተፈ ከ25 ተማሪዎች መረጃ ተሰብስቦ የተገኘው መረጃ በክሮንባኽ አሌፊ ተሰሌቶ ውጤቱን ከ0.7 በሊይ በመሆኑ ሇመረጃ መሰብሰቢያነት አገሌግሎሌ፡፡ በቅዴመትምህርት ፇተናው የተገኘው ውጤት በቁጥጥርና በሙከራ ቡዴን ተማሪዎች አማካይ ውጤት መካከሌ ጉሌህ የሆነ ስታትስቲካዊ ሌዩነት ባሇማሳየቱ ፍትነቱ ተካሂዶሌ፡፡ ከፍትነት በኋሊ ተጠኚ ተማሪዎች የዴህረትምህርት ፇተናውን ተፇትነዋሌ፡፡ በፇተናው ያስመገቡት አማካይ ውጤት የቁጥጥር ቡዴን 12.563፣ የሙከራ ቡዴን 14.404 ነው፡፡ በሁሇቱ ቡዴኖች አማካይ ውጤቶች መካከሌ ያሇው ሌዩነት ስታተስቲካዊ ጉሌህ መሆኑን ሇመፇተሽ በተዯረገው የነጻ ናሙና ቲቴስት ፍተሻ በተገኘው ውጤት መሰረት (t(93) = -3.462, P = 0.001) በቡዴኖቹ መካከሌ ጉሌህ ሌዩነት መኖሩን አሳይቷሌ። በመሆኑም ይት ተኮር የሰዋስው ትምህርት የሰዋስው እውቀትን የመጨመር ፊይዲ እንዲሇው መረዲት ተችሎሌ፡፡ ማስተማሪያ ዳው የሰዋስው እውቀትን ከመጨመር አንጻር ያሇውን የተጽዕኖ መጠን ሇመፇተሽ በተዯረገው የኮህን ዱ ፍተሻ ከፍተኛ ተጽዕኖ (d = 0.71) እንዲሇው ማረጋገጥ ተችሎሌ፡፡ ከጥናቱ ውጤት በመነሳት መምህራን የተማሪዎችን የሰዋስው እውቀት ሇማዲበር ይት ተኮር ዳን ቢተገብሩ፣ በሥርዓተ ትምህርት ዜግጅት ወይም ማሻሻሌ ሊይ የሚሰሩ ባሇሙያዎች የሰዋስው ትምህርትን አቀራረብና ማስተማሪያ ዳ ሲያጋጁ ሇይት ተኮር ዳ ትግበራ ምቹ የሆኑ አቀራረቦችንና ማስተማሪያ ዳዎችን ቢያካትቱ፣ በሰዋስው ማስተማሪያ ዳዎች ሊይ ምርምር ማዴረግ የሚፇሌጉ ተመራማሪዎች አማርኛን እንዯሁሇተኛ ቋንቋ በሚማሩ ተማሪዎች ሊይ ምርምር ቢያዯርጉ የሚለ የጥናት ጥቆማና አስተያየቶች በአጥኚው ቀርበዋሌ፡፡Item የመኤኒት ብሔረሰብ ሚት ማኅበረሰባዊ ፋይዳ(Addis Ababa University, 2014-06-23) አንዱዓለም አባተ; ዘሪሁን አስፋዉ (ተባባሪ ፕሮፌሰር)የመኤኒት ብሔረሰብ በዯቡብ ክሌሌ፣ በቤንች ማጂ ዝን ውስጥ የሚገኝ ብሔረሰብ ነው፡፡ የብሔረሰቡ አባሊት በዋናነት በመኤኒት ጎሌዱያ እና በመኤኒት ሻሻ ወረዲዎች ሲገኙ፣ በጥቂቱም ቢሆን በጉራ ፇርዲ እና በአንዲንዴ አጎራባች ወረዲዎች ውስጥ ይኖራለ፡፡ የመኤኒት ብሔረሰብን ታሪክ፣ ባሕሌና እሴቶችን ሇመረዲት ይህ ጥናት የብሔረሰቡ ሚትና ፊይዲ ያተኩራሌ፡፡ ሚትን አስመሌክቶ በብሔረሰቡ ሊይ የተጠኑ ጥቶች አሇመኖራቸው ይሄንን ጥናት ሇማዴረግ ዏቢይ ምክንያት ሲሆን፣ ጥናቱን የተሳካ እንዱሆንም መረጃዎች በቀዲማይ እና በካሌአይ የመረጃ ምንጮች ተሰብስበዋሌ፡፡ የተሰበሰቡት መረጃዎች በተረካዊ እና በመዋቅራዊ ንዴፇ ሀሳቦች ተተንትነዋሌ፡፡ ይህ ጥናት ዋና ዋና የመኤኒት ብሔረሰብ ሚቶችን ሇይቷሌ፡፡ እነሱም የአፇጣጠር ሚት፣ የመንፇሳዊ ሚት፣ የመስተጋዴሊውያን ሚትና የዲግም ውሌዯት ሚት ናቸው፡፡ በጥናቱ በየሚቶቹ ውስጥ የሚገኙ ትዕምርቶች በትንተናው ወቅት ተፇክረዋሌ፡፡ የብሔረሰቡ አባሊት ሇሚቶቹ ያሊቸው አመሇካከትም ተብራርቷሌ፡፡ እነዙህ ሚቶችም ሇብሔረሰቡ የሚሰጧቸው ሌዩ ሌዩ ፊይዲዎችም እንዱሁ በጥናቱ ግኝት ውስጥ ቀርበዋሌ፡፡ የብሔረሰቡ አባሊት ሇሚያነሷቸው ሇዒሇማዊ ጥያቄዎች መሌስ በመስጠት የብሔረሰቡ ሚቶች የብሔረሰቡን ሌዩ ሌዩ ባሕልች፣ ታሪኮች፣ ሃይማኖትን እና ዕሴቶች የመግሇጥ፣ የማስተማር፣ የመግታትና የመቆጣጠር፣ ማኅበረሰባዊ መዋቅርን የመገንባት፣ የሥሌጣን ክፌፌሌ እንዱኖር የማዴረግ፣ የተሇያዩ የኅብተረሰብ ክፌልችን አንዴ የማዴረግ ፊይዲዎች እንዲሊቸው በጥናቱ ተመሌክቷሌ፡፡ ይህ በመኤኒት ብሔረሰብ ሚት ፊይዲ ሊይ ያተኮረው ጥናት ብሔረሰቡ ፀንቶ የቆመባቸውን እና የቡዴን ሕሊዌውን ያስጠበቀባቸው መሠረቶች አሳይቷሌ፡፡ የመኤኒት ብሔረሰብ ሚቶች እንዱጠበቁ፣ እንዱዲብሩ በሌማትና ዕዴገት ሊይ የሊቀ ሚና እንዱኖራቸው የሚመሇከታቸው አካሊት ዴጋፌ እንዱያዯርጉ የይሁንታ ሀሳብ በማቅረብ ጥናቱ ተጠናቋሌ፡፡Item በአማርኛ ቋንቋ ትምህርት በይት ተኮር ዳ ሰዋስውን ማስተማር የሰዋስው እውቀትን ሇማዲበር ያሇው ፊይዲ ፌተሻ(Addis Ababa University, 2017-06-01) አሸናፉ ደበበ; ሙለሰው አስራቴ (ድ/ር)የዙህ ጥናት ዋና ዓሊማ በአማርኛ ቋንቋ ትምህርት በይት ተኮር ዳ ሰዋስውን ማስተማር የሰዋስው እውቀትን ሇመጨመር ያሇው ፊይዲ ምን ያህሌ እንዯሆነ መፇተሸ ነው፡፡ ይህን ዓሊማ ሇመሳካት ጥናቱ ፍትነት መሰሌ ቅዴመና ዴሕረትምህርት ባሇቁጥጥር ቡዴን ንዴፍን ተከትሎሌ፡፡ ሇዙህም የቃሉቲ ሁሇተኛ ዯረጃ ትምህርት ቤትና የክፍሌ ዯረጃው (አስረኛ ክፍሌን) በአመቺ የንሞና ዳ፣ ሁሇት መማሪያ ክፍልችን (10B እና 10E) በቀሊሌ የእጣ ንሞና ስሌት እንዱሁም በመማሪያ ክፍልቹ የሚማሩ 95 ተማሪዎች በጠቅሊይ የንሞና ስሌት በጥናቱ ተሳታፉነት ተመርጠዋሌ፡፡ ከ95 ተማሪዎች መረጃ የተሰበሰበው በቅዴመና ዴሕረትምህርት የሰዋስው እውቀት መሇኪያ ፇተና ነው፡፡ አስተማማኝነቱን ሇመፇተሽም በዋናው ጥናት ባሌተሳተፈ ከ25 ተማሪዎች መረጃ ተሰብስቦ የተገኘው መረጃ በክሮንባኽ አሌፊ ተሰሌቶ ውጤቱን ከ0.7 በሊይ በመሆኑ ሇመረጃ መሰብሰቢያነት አገሌግሎሌ፡፡ በቅዴመትምህርት ፇተናው የተገኘው ውጤት በቁጥጥርና በሙከራ ቡዴን ተማሪዎች አማካይ ውጤት መካከሌ ጉሌህ የሆነ ስታትስቲካዊ ሌዩነት ባሇማሳየቱ ፍትነቱ ተካሂዶሌ፡፡ ከፍትነት በኋሊ ተጠኚ ተማሪዎች የዴህረትምህርት ፇተናውን ተፇትነዋሌ፡፡ በፇተናው ያስመገቡት አማካይ ውጤት የቁጥጥር ቡዴን 12.563፣ የሙከራ ቡዴን 14.404 ነው፡፡ በሁሇቱ ቡዴኖች አማካይ ውጤቶች መካከሌ ያሇው ሌዩነት ስታተስቲካዊ ጉሌህ መሆኑን ሇመፇተሽ በተዯረገው የነጻ ናሙና ቲቴስት ፍተሻ በተገኘው ውጤት መሰረት (t(93) = -3.462, P = 0.001) በቡዴኖቹ መካከሌ ጉሌህ ሌዩነት መኖሩን አሳይቷሌ። በመሆኑም ይት ተኮር የሰዋስው ትምህርት የሰዋስው እውቀትን የመጨመር ፊይዲ እንዲሇው መረዲት ተችሎሌ፡፡ ማስተማሪያ ዳው የሰዋስው እውቀትን ከመጨመር አንጻር ያሇውን የተጽዕኖ መጠን ሇመፇተሽ በተዯረገው የኮህን ዱ ፍተሻ ከፍተኛ ተጽዕኖ (d = 0.71) እንዲሇው ማረጋገጥ ተችሎሌ፡፡ ከጥናቱ ውጤት በመነሳት መምህራን የተማሪዎችን የሰዋስው እውቀት ሇማዲበር ይት ተኮር ዳን ቢተገብሩ፣ በሥርዓተ ትምህርት ዜግጅት ወይም ማሻሻሌ ሊይ የሚሰሩ ባሇሙያዎች የሰዋስው ትምህርትን አቀራረብና ማስተማሪያ ዳ ሲያጋጁ ሇይት ተኮር ዳ ትግበራ ምቹ የሆኑ አቀራረቦችንና ማስተማሪያ ዳዎችን ቢያካትቱ፣ በሰዋስው ማስተማሪያ ዳዎች ሊይ ምርምር ማዴረግ የሚፇሌጉ ተመራማሪዎች አማርኛን እንዯሁሇተኛ ቋንቋ በሚማሩ ተማሪዎች ሊይ ምርምር ቢያዯርጉ የሚለ የጥናት ጥቆማና አስተያየቶች በአጥኚው ቀርበዋሌ፡፡Item የክቡር ዶክተር ሀዲስ ዓለማየሁ የሕይወት ታሪክና የስነፅሑፍ ስራዎቻቸው(አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 1992) ፈለቀች እሸቴ; ዘሪሁን አስፋውየክቡር ዶክተር ሀዲስ ዓለማየሁ የሕይወት ታሪክItem የአርጐባ ብሄረሰብ የወሊድ፣ የጋብቻና የሀዘን ስነ ስርዓቶች ክዋኔ ትንተና፤ በአፋር ክልል፣ ዞን ሶስት፣ አርጐባ ልዩ ወረዳ(2017-08-16) እታገኘሁ አስረስ; ዘሪሁን አስፋው (ተባባሪ ኘሮፌሰር)የፎክሎር አንድ ክፍል የሆነው ሀገረሰባዊ ልማድ ከሚይዛቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ ስነ ስርዓት (Ritual) ነው፡፡ ከስነ ስርዓት ዓይነቶች መካከል ደግሞ የህይወት ሽግግር ስነ ስርዓቶች ይገኛሉ፡፡ ይህ ጥናት በህይወት ሽግግር ስነ ስርዓቶች ላይ ትኩረት ያደረገ ሲሆን "የአርጐባ ብሄረሰብ የወሊድ፣ የጋብቻና የሀዘን ስነ ስርዓቶች ክዋኔ ትንተና፤ በአፋር ክልል፣ ዞን ሶስት፣ አርጐባ ልዩ ወረዳ" በሚል ርዕስ የቀረበ ነው፡፡ የጥናቱ ዋና ዓላማ በአፋር ክልል ከሚኖረው የአርጐባ ብሄረሰብ የህይወት ሽግግር ስነ ስርዓቶች መካከል የወሊድ፣ የጋብቻና የሀዘን ስነ ስርዓቶችን ክዋኔ መተንተን ነው፡፡ በአፋር ክልል የሚኖረውን የአርጐባ ብሄረሰብ የወሊድ፣ የጋብቻና የሀዘን ስነ ስርዓቶች ለመተንተን የክዋኔ፣ መዋቅራዊ፣ ትዕምርታዊና ተግባራዊ ንድፈ ሀሳቦች ጥቅም ላይ የዋሉ ሲሆን የጥናቱን ዓላማ ለማሳካትና የምርምር ጥያቄዎችን ለመመለስ ካልዓይና ቀዳማይ መረጃዎች ተሰብስበዋል፡፡ ካልዓይ መረጃ ከጽሁፍ ሰነዶች፣ ቀዳማይ መረጃ ደግሞ የመስክ ስራ በማከናወን የተሰበሰበ ሲሆን በመስክ መረጃን ለመሰብሰብ ጥቅም ላይ የዋሉ ምልከታ፣ ቃለመጠይቅና ቡድን ተኮር ውይይት ዘዴዎች ናቸው፡፡ የጥናት ቦታና የመረጃ ሰጪ መረጣ የተከናወነው በአላማ ተኮርና በጠቋሚ የንሞና ዘዴ ነው፡፡ መረጃ የተሰበሰበባቸው አውዶች ተፈጥሯዊና አርቴፊሻል አውዶች ሲሆኑ መረጃው ከዓይነታዊ የመረጃ መተንተኛ ዘዴዎች ውስጥ ኢትኖግራፊ የጥናት ሞዴልን በመጠቀም ተተንትኗል፡፡ የሜታ ፎክሎር ምርመራም በመረጃ መተንተኛነት ጥቅም ላይ ውሏል፡፡ የጥናቱ ግኝት እንደሚያሳየው በአፋር ክልል የሚኖረው የአርጐባ ብሄረሰብ የጋብቻ ስነ ስርዓት ክዋኔ መዋቅር በቅድመ መለየት፣ መለየት፣ ሽግግርና መቀላቀል ደረጃዎች ሊከፈል የሚችል ሲሆን የወሊድና የሀዘን ስነ ስርዓቶች ክዋኔዎች ደግሞ በመለየት፣ ሽግግርና መቀላቀል ደረጃዎች ሊከፈሉ የሚችሉ ናቸው፡፡ በብሄረሰቡ የወሊድ ስነ ስርዓት ክዋኔ ስነቃል (ዱዓዎች፣ ዝኪሮች)፣ ቁሳዊ ባህል (ሽታ፣ አዝጋሮ፣ ወይባ፣ አልባሳት) እና ሀገረሰባዊ ልማድ (እምነቶች፣ ባህላዊ ሕክምና፣ ጭስ መሞቅ) ፎክሎሮች ተለይተዋል፡፡ በጋብቻ ስነ ስርዓት ክዋኔ ስነቃል (ቃል ማሰሪያዎች፣ መወከያዎች፣ ዱዓዎች)፣ ቁሳዊ ባህል (ወይደል፣ ምግብና መጠጥ፣ አልባሳት፣ ጌጣጌጥ፣ ጉፍታ)፣ ሀገረሰባዊ ልማድ (እምነቶች፣ ጭስ መሞቅ) እና ሀገረሰባዊ ትውን ጥበባት (ሺሎ፣ ዘፈኖች) ፎክሎሮች ተለይተዋል፡፡ በሀዘን ስነ ስርዓት ክዋኔም ስነቃል (ዱዓ፣ ማጽናኛዎች፣ መሰናበቻዎች)፣ ቁሳዊ ባህል (ምግብና መጠጥ፣ የከፈን ጨርቅ፣ ማግ፣ መዋስ) እና ሀገረሰባዊ ልማድ (ባህላዊ ህክምና፣ እምነት) ፎክሎሮች ተለይተዋል፡፡ በብሄረሰቡ በወሊድ ስነ ስርዓት ክዋኔ ውስጥ ያሉ ቃላዊ (የዱዓ ቃላት)፣ ቁሳዊና (ማር) ድርጊታዊ (ጣትን በገበታ ዙሪያ ማድረግ፣ ገበታን ከፍ ማድረግ፣ ድፍን ቅል አልጋ ላይ ማድረግ)፣ በጋብቻ ስነ ስርዓት ክዋኔ ውስጥ ያሉ ቃላዊ (የዱዓ ቃላት)፣ ቁሳዊ (የወይደል ቀለም፣ ጉፍታ) እና ድርጊታዊ (ለሙሽራ ጉፍታ የምትጭን ሴት አግብታ ያልፈታች መሆኗ) እና በሀዘን ስነ ስርዓት ክዋኔ ውስጥ ያሉ ድርጊታዊና (ጥልፍ መተርተር፣ ውሀ ማርከፍከፍና እርጥብ ቅጠል መጐዝጐዝ፣ መዋስን በጠዋት ውሀ አርከፍክፎ ማጠፍ፣ እጅንና ፊትን በቀዝቃዛ ውሃ መታጠብ) ቁሳዊ (ውሀ፣ መዋስ) ትዕምርቶች ተለይተዋል፡፡ የብሄረሰቡ የወሊድ ስነ ስርዓት ማህበራዊና (ወላድ መንከባከብ፣ አራስ መጠየቅ) ስነ ልቡናዊ (ባህላዊ ህክምናና የአምሮት ስነ ስርዓት) ፋይዳዎች አሉት፡፡ የብሄረሰቡ የጋብቻ ስነ ስርዓት የአሻጋሪነት (ትዳር የሌለውን ሰው ወደ ባለትዳርነት)፣ ማህበራዊ (ሰዎችን በአንድ ያገናኛል)፣ ኢኮኖሚያዊ (ስጦታዎች)፣ ስነ ልቡናዊና (ዱዓና ባዷሼህ) የተግባቦትና የማዝናናት (ዘፈኖች) ፋይዳዎች አሉት፡፡ የብሄረሰቡ የሀዘን ስነ ስርዓት ተግባቦታዊና ማህበራዊ (ለቅሶ መድረስ)፣ ኢኰኖሚያዊና (ሀፈሻ) ስነ ልቡናዊ (በጋራ ማልቀስና ሶደቃ) ፋይዳዎች አሉት፡፡ ለውጥን ተቋቁመው የቀጠሉ ክዋኔዎች ቢኖሩም በብሄረሰቡ የወሊድና የሀዘን ስነ ስርዓቶች ላይ የክዋኔ ለውጦች፤ በብሄረሰቡ የጋብቻ ስነ ስርዓት ላይ ደግሞ የክዋኔና የመዋቅር ለውጦች ታይተዋል፡፡ ምሳሌያዊ አነጋገሮች ተለይተው የሜታ ፎክሎር ምርመራም ተደርጐባቸዋል፡፡ በጋቸኔ ጤና ጣቢያ የተሰራው ባህላዊ ጐጆ ለታሰበለት ዓላማ ቢውል፣ የነፍሰጡር የምግብ ክልክሎችና ከነፍሰጡሯ ጤና አንፃር ጉዳት ያለው መሆኑና አለመሆኑ ቢጠና፣ በወሊድ ጊዜ የሚከወኑ አንዳንድ ክዋኔዎች ለምሳሌ፣ መነቅነቅ የሚያስከትሏቸው የጤና ጉዳቶች ካሉ በጥናት ቢለዩ፣ ሀፈሻን ከዘመናዊ የመረዳጃ ተቋማት ጋር ማስተሳሰር ቢቻል፣ ዚያራ በዝርዝር ቢጠና ጥሩ ነው፡፡Item የድጋፍ ብልሃቶች በአንብቦ የመረዳት ችሎታ እና ግለመር ማንበብ ላይ ተፅዕኖ፤ በ7ኛ ክፍል ተማሪዎች ተተኳሪነት(አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ, 2016) ራሔል ሲሳይ ተገኘ; ፕሮፌሰር ተስፋየ ሸዋየየዚህ ጥናት ዓላማ የድጋፍ ብልሃቶች የተማሪዎችን በአማርኛ ቋንቋ አንብቦ የመረዳት ችሎታ እና ግለመር ማንበብ ላይ ያላቸውን ተፅዕኖ መፈተሸ ነበር፡፡ ጥናቱ በዓይነቱ ቅደምተከተላው ቅይጥ (በአመዛኙ መጠናዊ) ሲሆን ቅድመና ድህረ ትምህርት በለቁጥጥር ቡድን ፍትነት ቡድን ፍትነት መሰል ንድፍን የተከተለ ነው፡፡ በ2015 ዓ.ም በአዲስአበባ ከተማ አስተዳደር፡ በጉለሌ ክፍለ ከተማ በአድስተስፋ አንደኛ ደረጃ ትምህርትቤት የ7ኛ ክፍል ተማሪዎች ተሳትፈዋል፡፡ መረጃዎችን ለመሰብሰብም አንብቦ የመረዳት ችሎታ ፈተናና የግለመር ማንበብ መጠይቅ ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡ ሌላው በአግዥነት ድህረቡድን ተኮር ውይይት ተግባራዊ ሆኗል ፡፡ እንዲሁም ሁለቱ ቡድኖች በተቀመጠላቸው የማስተማሪያ መንገድ መማርቸውን ለማረጋገጥ ሲባል ምልከታ ተካሂዷል ፡፡በቅድመ ፈተናና መቅድመ የጽሑፍ መጠይቅ የተገኙ ውጤቶች በጥንድና ነፃ ቲ-ትስቶች የትንተና ስልት እንዲሁም በድኀረ ፈተናና በድኀረ የጽሑፍ መጠይቅ የተገኙ ውጤቶች በጥንድ፡ ነፃ ቲ- ትስቶችና በአበር ልይይት ትንተና ስልቶች ተተንትነዋል፡፡ በተጨማሪም ከድህረቡድን ተኮር ውይይት የተገኙት ውጤቶችም እንደሚያመለክቱት በቅድመፈተናና በቅድመየጽሑፍ መጠይቅ ቡድኖች ተመጣጣኝ አማካይ ውጤቶች ያስመዘገቡ ሲሆን በድኀረ የጽሑፍ መጠይቅ ገለመር ማንበብ የሙከራ ቡድኑ ተማሪዎች ከቁጥጥት ቡድኑ ተማሪዎች ጉልህ የሆነ ልዩነት አሳይተዋል (P= <0.05):: ይህም ውጤት በድጋፍ ብልሀቶች መማር የተማሪዎችን አንብቦ የመረዳት ችሎታና ግለመር ማንበብን ከማሻሻል አኳያ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቁሟል፡፡ በተገኙት ውጤቶች በመመስረት የመፍትሄ ሀሳቦችና የጥናት ጥቆማዎች ተሰጥተዋል፡፡Item የስሜታዊ ብልህነት፣ የመጻፍ ችሎታና የመጻፍ ተነሳሽነት ፆታተኮር ተዛምዶ፤ በ11ኛ ክፍል ተማሪዎች ተተኳሪነት(አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ, 2016) በለጠ ሕሉፍ ኪሮስ; ፕሮፌሰር ጌታሁን አማረየጥናቱ ዋና ዓላማ የስሜታዊ ብልህነት፣ የመጻፍ ችሎታና የመጻፍ ተነሳሽነት ያላቸውን ተዛምዶ ከጾታ አንጻር መፈተሽ ነበር፡፡ ዓላማውን ለማሳካትም ጥናቱ በተለዋዋጮቹ መካከል ያለውን ዝምድና የማሳየት አላማ ስላለው የተከተለው ዲዛይን (ስልት) ተዛምዷዊ ነበር፡፡ የጥናቱ ተሳታፊዎች በ2013 ዓ.ም በደሴ ከተማ አስተዳደር የሁለተኛ ደረጃ የሁለተኛው ሳይክል ካላቸው ትምህርትቤቶች መካከል በመምህር አካለወልድ የነበሩ ከ11ኛ G እስከ L ክፍል የማኅበራዊ ሳይንስ (107 ወንዶችና 69 ሴቶች በአጠቃላይ 176) ተማሪዎች በቀላል የዕጣ ንሞና ዘዴ የተወሰዱ ናቸው፡፡ ከተሳታፊዎቹ፤ የስሜታዊ ብልህነት መጠይቅና የመጻፍ ተነሳሽነት መጠይቅ እንዲሞሉ እንዲሁም የመጻፍ ችሎታን ለመፈተሽ የሚያገለግል የመጻፊያ ርእስ በመስጠት እንዲጽፉ በማድረግ መረጃዎች ተሰብስበዋል፡፡ የተገኙት መረጃዎችም በገላጭ ስታትስቲክስ (በአማካይ ውጤትና በመደበኛ ልይይት)፣ የርስበርስና የጠራ ዝምድናቸውን ለመለየት በፒርሰን የተዛምዶ መለኪያ እንዲሁም በከፊል የተዛምዶ መፈተሻ ዘዴ ተሰልተው ተተንትነዋል፡፡ የጥናቱ ውጤቶች እንዳመላከቱትም በስሜታዊ ብልህነት፣ በመጻፍ ችሎታና በመጻፍ ተነሳሽነት መካከል ጾታተኮር ዝምድና ታይቷል፡፡ በሌላ በኩል የስሜታዊ ብልህነት ዘርፎች ከመጻፍ ችሎታ ጋር ተዛምዷቸው ከጾታ አንጻር ልዩነት አላቸው፡፡ እንዲሁም የስሜታዊ ብልህነትና የመጻፍ ችሎታ ከተነሳሽነት አንጻር ልዩነት አሳይተዋል፡፡ በመጻፍ ችሎታና በመጻፍ ተነሳሽነት መካከል ጾታን መሰረት አድርጎ ልዩነት አልታየም፡፡ ከጥናቱ ግኝቶች በመነሳትም ጾታ ጣልቃገብ ሲሆን በተላውጦዎቹ መካከል ልዩነት ያሳያል ወደሚልና የስሜት ብልህነትና የመጻፍ ችሎታ ተዛምዶ የሚኖራቸው የመጻፍ ተነሳሽነት ሲኖር ነው ወደሚል ድምዳሜ ተደርሷል፡፡ ከጥናቱ ግኝቶች በመነሳትም አስተያየቶች ተጠቁመዋል፤ የወደፊት የምርምር አቅጣጫዎችም ተመላክተዋል፡፡Item ፕሮጀክት ተኮር መማር፣ በመጻፍ ችሎታና ተነሳሽነት ላይ ያለው ተፅዕኖ፤ በ10ኛ ክፍል አማርኛ ቋንቋ አፍፈት ተማሪዎች ተተኳሪነት(አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ, 2016) በስመኝ አለምነህ; ጌታሁን አማረ (ፕ/ር); ግርማ ገብሬ (ዶ/ር)የዚህ ጥናት ዓላማ ፕሮጀክት ተኮር መማር፣ ለተማሪዎች የመጻፍ ችሎታእናተነሳሽነትመሻሻል ያለውን ሚና መፈተሽ ነው፡፡ ዓላማውን ከግብ ለማድረስምቅድመትምህርትናድኅረ ትምህርት ፈተና ባለቁጥጥር ቡድን ከፊል ሙከራዊ (quasi-expermental) ስልትተግባራዊ ሆኗል፡፡ በጥናቱ የትግበራ ሂደትም አማራ ክልል በአላማተኮርንሞናተመርጧል፤ ደብረማርቆስ ከተማ የሚገኘው ንጉስ ተክለሃይማኖትአጠቃላይሁለተኛደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ደግሞ በአመቺ ንሞና ከተመረጠበኋላ በዚህትምህርትቤት የሚገኙ የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች በዕጣ ተመርጠው ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ ክልሉበዓላማተኮር ንሞና የተመረጠው ጥናቱ አፍፈት ተማሪዎች ላይ የሚያተኩርበመሆኑነው።ትምህርት ቤቱ በአመቺ ንሞና የተመረጠበት ምክንያትምጥናቱከፊልፍትነታዊእንደመሆኑ መጠን ትምህርት ቤቱን እና የአማርኛ ቋንቋ መምህራንን ልዩትብብርእናድጋፍ የሚፈልጉ ጉዳዮችን የሚጠይቅ በመሆኑ ለዚህም የትምህርትቤቱአስተዳደር፣መምህራንና ተማሪዎች ለጥናቱ ፈቃደኛ በመሆናቸው ነው፡፡ የ10ኛ ክፍልተማሪዎችበዕጣየተመረጡበት ምክንያት ደግሞ ከ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በስተቀር ጥናቱበ9ኛ፣ 10ኛእና11ኛ ክፍል ተማሪዎች ላይ ቢካሄድ በተማሪዎች መረጃ የመሰብሰብሂደትላይችግርአይኖርም ተብሎ ስለታሰበ ነው፡፡ መረጃዎች ከተሳታፊ ተማሪዎችበመጻፍችሎታፈተናእና በመጻፍ ተነሳሽነት የጽሑፍ መጠይቅ ተሰብስበዋል፡፡ የተገኙትመረጃዎችምየመተንተኛ ስልቱ እሙኖች በገላጭ ስታቲስቲክስ ከተፈተሹ በኋላ በሙከራናበቁጥጥርቡድኖች መካከል ልዩነት መኖር አለመኖሩን ለመፈተሽ የቅድመና ድኅረትምህርትአጠቃላይ የመጻፍ ችሎታ፣ ንዑሳን ችሎታዎች (ይዘት፣ አደረጃጀት፣ የቃላትአመራረጥናአጠቃቀም፣ የቋንቋ አጠቃቀም እና ስርዓተ አጻጻፍ) አማካይ ውጤቶችና የመጻፍተነሳሽነትየጽሑፍ መጠይቅ አማካይ ውጤቶች በባለብዙ ተላውጦ ልይይትትንተናዘዴ(Multivariate Analysis of Variance, MANOVA) ተሰልተውተተንትነዋል፡፡ በተገኙትውጤቶች መሠረትም፣ የተማሪዎች አጠቃላይ የመጻፍ ችሎታእና ንዑሳንችሎታዎች(ይዘት፣ አደረጃጀት፣ የቃላት አመራረጥና አጠቃቀም፣ የቋንቋ አጠቃቀምእናስርዓተአጻጻፍ) እንዲሁም የመጻፍ ተነሳሽነት የጽሑፍ መጠይቅ ውጤቶችየሙከራቡድንተማሪዎች ከቁጥጥር ቡድን ተማሪዎች አማካይ ውጤቶች ተሽለውና ጉልህ (p<.05) ልዩነትያላቸው ሆነው ተገኝተዋል። በዚህም መሠረት ፕሮጀክት ተኮር መማርየተማሪዎችንአጠቃላይ የመጻፍ ችሎታ እና ንዑሳን ችሎታዎች እንዲሁም የመጻፍተነሳሽነትለማሻሻልሚና እንዳለውና ሚናውም ከፍተኛ እንደሆነ ጥናቱ አሳይቷል፡፡ በመሆኑም፣ የመጻፍትምህርትን በፕሮጀክት ተኮር መማር ተግባራት ማቅረብ እንደሚያስፈልግተጠቁሟል፡፡Item የአፍ መፍቻ ቋንቋን በትምህርት መስጫነት የመጠቀም አመለካከቶችና ተግዳሮቶች፤ በስልጤ፣ በሀድያ፣ በከምባታና በወላይታ ቋንቋዎች ተተኳሪነት(አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ, 2010) በጎሰው የሽዋስ መንግስት; ፕ/ር ባየ ይማምየጥናቱ ዋና ዓላማ የአፍ መፍቻ ቋንቋን በትምህርት መስጫነት በመጠቀም ረገድ እየታዩ ያሉ አመለካከቶችንና እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶችን ማጥናት ነው፡፡ ዓላማውን ለማሳካትም የጥናቱ ንድፍ ውህድ ዘዴን የተከተለ ሲሆን ከውህድ ጥናት ንድፍ ንኡስ ክፍሎችም ባለትይዩ አቻ ውህድ ዘዴ (convergent parallel mixed method) ተግባራዊ የተደረገበት ነው፡፡ ለጥናቱ አስተማማኝ መረጃዎችን ለማግኘትም ቅንጅታዊ የምርምር ዘዴ ተግባራዊ ተደርጓል፡፡ የጥናቱ ቦታም የደቡብ ኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልልን ሲሆን፣ በዚህ ክልል ውስጥ “medium MT exit model”ን (ከአንደኛ እስከ አራተኛ ክፍል) ከሚጠቀሙ ዞኖች መካከል ስልጤን፣ ወላይታን፣ ከምባታንና ሀድያን በእጣ ንሞና በመምረጥ በጽሁፍና በቃል መጠይቅ መረጃ ተሰብስቧል፡፡ በእነዚህ ዞኖች ውስጥም በ18 የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ በስምንት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ በሁለት የመምህራን ኮሌጆች፣ በስምንት የገጠርና የከተማ ቀበሌዎች፣ በ12 የዞንና የወረዳ ትምህርት መምሪያዎች ከወላጆች፣ ከመምህራን፣ ከተማሪዎች፣ ከትምህርት ባለሞያዎችና ሀላፊዎች መረጃ ተሰብስቧል፡፡ የተገኙ መረጃዎችም በየንዑስርዕሰ ጉዳዮች ስር ተደራጅተው በገላጭ የትንተና ስልት ተተንትነዋል፡፡ ትንተናውን ለማካሄድም የማህበራዊ ሳይንስ ጥናት መረጃዎችን ለመተንትን የተዘጋጀው የኮምፒተር ፕሮግራም SPSS /Statistical Package for the Social Science/ ጥቅም ላይ ውሏል፡፡ የጥናቱ ግኝቶች እንዳመለከቱትም አብዛኞቹ የጥናቱ ተተኳሪዎች የአንደኛ ደረጃ ትምህርት በአፍ መፍቻ ቋንቋ በመሰጠቱ ደስተኞች እንደሆኑና እንደሚደግፉ ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡ ከአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (ከአንደኛ እስከ አራተኛ ክፍል) ባለፈ ግን ለትምህርት መስጫነት ከአፍ መፍቻ ቋንቋ ይልቅ እንግሊዝኛን እንደሚመርጡ ለማወቅ ተችሏል፡፡ የአመለካከቶቹ መንስኤዎችም ባብዛኛው ኢኮኖሚያዊ፣ ስነትምህርታዊና ስነልቦናዊ ሆነው ተገኝተዋል፡፡ ሌላው የተግዳሮት ጉዳይ ሲሆን፣ በአፍ መፍቻ ቋንቋ በማስተማር ሂደት ላይ አብይ ተግዳሮት ሆኖ በዚህ ጥናት የተገኘው ስነትምህርታዊ ተግዳሮት ነው፡፡ የዚህም መንስኤው ባብዛኛው የፖለቲካ ቁርጠኝነት አለመኖር እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በመጨረሻም ከጥናቱ ግኝቶች በመነሳት አስተያየቶች ቀርበዋል፡፡ የወደፊት የምርምር አቅጣጫዎችም ተጠቁመዋል፡፡Item ትብብራዊ መማር የተማሪዎችን የመፃፍ ክሂል፣ ማህበራዊ ክሂልና የመፃፍ ተነሳሽነት ለማሳደግ ያለው ሚና (አማርኛን በሁለተኛ ቋንቋነት በሚማሩ በባሌ ዞን በዘይበላ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ7ኛ ክፍል ተማሪዎች ተተኳሪነት)(አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ, 2009) ግርማ ኃይሉ; ዶ/ር ጌታቸው እንዳላማውየጥናቱ ዓላማ ትብብራዊ መማር የተማሪዎችን የመፃፍ ክሂል፣ ማህበራዊ ክሂልና የመፃፍ ተነሳሽነት ለማሳደግ ያለውን ሚና መፈተሽ ነው፡፡ ጥናቱም የተከናወነው አማርኛን በሁለተኛ ቋንቋነት በሚማሩ በባሌ ዞን በዘይበላ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ7ኛ ክፍል ተማሪዎች ተተኳሪነት ነው፡፡ ጥናቱ ከፊል ፍትነታዊነት መሰል የምርምር (Quasi Experimental Research) ስልትን ተከትሏል፡፡ የመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያዎቹም ፈተና፣ የጽሑፍ መጠይቅና ቃለመጠይቅ ናቸው፡፡ የፈተናዎቹ ውጤት በt- ቴስት አማካይነት ተነጻጽሯል፡፡ ውጤቱንም ለማነጻጸር የስህተት ይሁንታ መጠኑ በ0.05 (5%) ባለሁለት ጫፍ ነው፡፡ ከዋናው ጥናት በፊት የቁጥጥር ቡድኑና የሙከራ ቡድኑ የነበራቸውን የቅድመሙከራ የመጻፍ ክሂል ችሎታ ከወዲሁ ለማወቅ የቅድመትምህርት ፈተና ተፈትነዋል፡፡ በቅድመትምህርት የፈተና ውጤታቸውም በአማካይ የቁጥጥር ቡድኑ 52.67 እንደዚሁም የሙከራ ቡድኑ 52.42 ሆኗል፡፡ ይህ ውጤት ሁለቱም ቡድኖች በድህረትምህርት ፈተና የመጻፍ ችሎታቸው ተቀራራቢ መሆኑን ጠቁሟል፡፡ በቀጣይ የቁጥጥር ቡድኑ በተለመደው መንገድ፣ የሙከራ ቡድኑ በትብብራዊ መማር ለአንድ ሴሚስተር ያህል ከተማሩ በኋላ ሁለቱም ቡድኖች የድህረትምህርት ፈተና ተፈተኑ፡፡ የተሳታፊዎቹ የድህረትምህርት ፈተና ውጤት በአማካይ የቁጥጥር ቡድኑ 53.13፣ እንደዚሁም የሙከራ ቡድኑ 59.38 ነው፡፡ ይህ የውጤት ልዩነት በt-ቴስት ስታትስቲክስ (p= 0.046) ጉልህ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ እንደዚሁም ትኩረት በተደረገባቸው ንዑሳን የመጻፍ ክሂሎች ላይ የሙከራ ቡድኑ የቅድመና የድህረትምህርት አማካይ የፈተና ውጤቶች ልዩነት በt-ቴስት ስታትስቲክስ ተሰልቶ ውጤቱም በተሰጡ ቃላትና ሀረጋት ዐረፍተነገር በማዋቀር ንዑስ ክሂል (p= 0.001)፣ የዐረፍተነገር ክፍሎችን ቅደም ተከተል በማስተካከል ንዑስ ክሂል (p= 0.00)፣ ጅምር ዐረፍተነገሮችን በማጠናቀቅ ንዑስ ክሂል (p= 0.000)፣ አያያዥ ቃላትን ተጠቅሞ ዐረፍተነገርን በማደራጀት ንዑስ ክሂል (p= 0.000)፣ ጅምር አንቀጽን በማጠናቀቅ ንዑስ ክሂል (p= 0.00) ጉልህ ሆኗል፡፡ በሌላ በኩል ትብብራዊ መማር የተማሪዎችን ማህበራዊ ክሂልና የመጻፍ ተነሳሽነትን ለማሳደግ ያለው ተፅዕኖ ምን እንደሚመስል በጽሑፍ መጠይቅና በቃለመጠይቅ አማካይነት መረጃ ተሰብስቧል፡፡ ማህበራዊ ክሂልን በተመለከተ የጽሑፍ መጠይቁን ከሞሉ መላሾች መካከል 81.18% የሚሆኑት ማህበራዊ ክሂላቸው እንዳደገ በምላሻቸው ጠቁመዋል፡፡ ይህም ውጤት በt- ቴስት ተሰልቶ 4.31 አማካይ ውጤት አሳይቷል፡፡ ይህ ውጤት ደግሞ Peta (2001) ባስቀመጠው ቀመር መሰረት ከፍተኛ ነው፡፡ ከቃለመጠይቁም የተገኘው ምላሽ የጽሑፍ መጠይቁን ውጤት የሚያጠናክር ሆኗል፡፡ እንደዚሁም የመጻፍ ተነሳሽነትን በተመለከተ የጽሑፍ መጠይቁን ከሞሉ መላሾች መካከል 83.83% የሚሆኑት የመጻፍ ተነሳሽነታቸው እንዳደገ በምላሻቸው ጠቁመዋል፡፡ ይህም ውጤት በt- ቴስት ተሰልቶ 4.4 አማካይ ውጤት አሳይቷል፡፡ አሁንም ይህ ውጤት Peta (2001) ባስቀመጠው ቀመር መሰረት ከፍተኛ ነው፡፡ ከቃለመጠይቁም የተገኘው ምላሽ የጽሑፍ መጠይቁን ውጤት የሚያጠናክር ሆኗል፡፡ በአጠቃላይ ከጽሑፍ መጠይቁና ከቃለመጠይቁ ከተገኘው መረጃ መገንዘብ የተቻለው ትብብራዊ መማር የተማሪዎችን ማህበራዊ ክሂልንና የመጻፍ ተነሳሽነትን ለማሳደግ ያለው ተፅዕኖ ጉልህ መሆኑን ነው፡፡ በመሆኑም ትብብራዊ መማር የተማሪዎችን የመፃፍ ክሂልን፣ ማህበራዊ ክሂልንና የመፃፍ ተነሳሽነትን ለማሳደግ ያለው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ፣ የሚመለከታቸው አካላት ለማስተማሪያ ዘዴው ትኩረት ሊሰጡት እንደሚገባ አጥኚው ይጠቁማል፡፡Item ሂደተ ዘውጋዊ ዘዴ በተማሪዎች ድርሰት የመፃፍ ችልታ እና አመለካከት ላይ የሚኖረው ተፅህኖ፣ በምዕራብ ሸዋ አካባቢ በኤጀሬ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ9ኛ ክፍል ተተኳሪነት(አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ, 2009) ተካልኝ ለማ; ዶ/ር ሴይመ ከበደItem የቤተሰብ ዳራ የአንብቦ መረዳት ችሎታን የመተንበይ ድርሻ፤ በአምስተኛና በሰባተኛ ክፍል ተማሪዎች ተተኳሪነት(አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ, 2010) አስቴር አስራት ዳኘው; ዶ/ር ታመነ ኪቲላ; ዶ/ር ሙላት አስናቀየዚህ ጥናት ዋና አላማ የቤተሰብ ዳራ የአንብቦ መረዳት ችሎታን የመተንበይ ድርሻውን መለየት ነው፡፡ ተሳታፊዎች በዶና በርበር የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2010 ዓ.ም ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ የሚገኙ በዕጣ ንሞና የተመረጡ 151 የአምስተኛና 170 የሰባተኛ ከፍል ተማሪዎች ናቸው፡፡ ከተሳታፊዎች መረጃ የተሰበሰበው በሶስት የተለያዩ የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴዎች ነው፡፡ እነሱም የጽሁፍ መጠይቅ፣ ፈተናና የቡድን ውይይት ናቸው፡፡ ፈተናው አንብቦ መረዳት ችሎታን፣ መጠይቁ የቤተሰብ ዳራን ለመለካት ሲያገለግል የቡድን ውይይቱ ደግሞ ተጨማሪ የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴ በመሆን አገልግሏል፡፡ የተሰበሰቡት መረጃዎች አስተማማኝነት፣ ተገቢነትና የውጤት ስርጭት ወጥነት ተሰልቶ ከተረጋገጠ በኋላ ሁሉም መረጃዎች በተንባይና ገላጭ ስታትስቲክሶች አማካኝነት ተተንትነው ተብራርተዋል፡፡ የተገኘው መረጃ የፓራሜትሪያዊ መፈተሻ ዘዴዎችን ለመጠቀም የሚያስችል በመሆኑ ተግባራዊ የተደረጉት የመተንተኛ ዘዴዎች የህብረ ድህረት ትንተናና የነጻ ናሙና ቲቴስት ናቸው፡፡ በትንተናው መሰረት የቤተሰብ ዳራ የአንብቦ መረዳት ችሎታን ጉልህ ተንባይ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ከቤተሰብ ዳራ ዝርዝር ተላውጦዎች የአንብቦ መረዳት ችሎታን በከፍተኛ ደረጃ የተነበዩት የቤተሰብ የኢኮኖሚ ደረጃና የቤተሰብ የትምህርት ደረጃ ናቸው፡፡ የቤተሰብ የኢኮኖሚ ደረጃ መለኪያ የሆኑት ወርሀዊ ገቢና ß= 0.5ና ገቢ ከአካባቢ ጋር ሲነጻጸር ß= 0.119 የቤተሰብ የትምህርት ደረጃ ß= 0.382 ከፍተኛ የመደበኛ ቤታ ዋጋ በማምጣት ከሌሎች ተላውዎች በተሻለ ጉልህ ተንባይ ሆነዋል፡፡ ይህ ውጤት በሁለቱም የክፍል ደረጃ ተቀራራቢ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ በተጨማሪነት የታየው ሌላው ጥያቄ የአንብቦ መረዳት ችሎታ በጾታ ልዩነት እንዳለው መቃኘት ሲሆን የወንዶች አማካኝ ችሎታ ከሴቶች የተሻለ ሆኖ ቢገኝም በሁለቱ መካከል ያለው ልዩነት ጉልህ እንዳልሆነ በትንተናው ተረጋግጧል፡፡ የአምስተኛ ክፍል ተማሪዎች ወንዶች 22.51 ሲሆን የሴቶቹ 21. 63 የሰባተኛ ክፍል ወንዶች 17.74 የሴቶች 17.13 ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ከዚህ ውጤት በመነሳትም በትምህርት ቤት ውስጥ የኢኮኖሚ ችግር ያለባቸውን ልጆች ድጋፍ ማድረግና ያልተማሩ ወላጆችን የተለያዩ የመሰረታዊ ትምህርት እንዲያገኙ ማድረግ የሚሉ የመፍትሄ ሀሳቦች ተሰጥተዋል፡፡ ለሴቶች የተለያዩ ድጋፎችን መስጠት የሚል ስነትምህርታዊ አንድምታ ተሰጥቷል፡፡ በተጨማሪም በረጅም ጊዜ የጥናት ስልት፣ ወላጆችንና መምህራንን ተሳታፊ በማድረግ፣ አጠቃላይ ከአንድ እስከ ስምንት የሚገኙ ተማሪዎችን በማካተት እንዲም በርካታ ናሙና ወስደው ማጥናት ይቻላል የሚሉ የምርምር ጥቆማዎችም ተሰጥተዋል፡፡Item መስተጋብራዊ የማስተማሪያ ዘዴ መስማት በተሳናቸው ተማሪዎች የመጻፍ ክሂሌ ችሎታና የመማር ፍላጎት ላይ ያለው ተጽዕኖ (በሰባተኛ ክፍል ላይ የተካሄደ ሙከራዊ ጥናት)(አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ, 2016) እታገኝ ገደፋው ጌታሁን; ዶ/ር ጌታቸው እንዳላማውየዚህ ጥናት ዋነኛ ዓላማ መስተጋብራዊ የማስተማሪያ ዘዴ መስማት የተሳናቸው ተማሪዎችን የመጻፍ ክሂሌ ችልታና የመማር ፍላጎት ከማሻሻል አንጻር ያለውን ተጽዕኖ መመርመር ነው፡፡ ጥናቱ በአንዴ የሙከራ ቡድን ንድፍ (Single Group Experimental Design) ላይ በመመስረት የተከናወነ ሲሆን ይህ የምርምር ንድፍም የጥናት ናሙናን በመምረጥ ሂደት የተጠኚዎች ቁጥር ለሁለት ቡድን ማለትም ለጥብቅ (Control) ለሙከራ (Exprmental) ሳይበቃ ሲቀር የሚመረጥ ነው፡፡ ጥናቱ የተካሄደው በአዱስ አበባ መስተዲድር ስር ከሚገኙ መስማት የተሳናቸው ተማሪዎች ትምህርት ቤቶች መካከል በአሌፋ መስማት የተሳናቸው ተማሪዎች የመጀመሪያ ደረጃ ልዩ ትምህርት ቤት ሲሆን በትምህርት ቤቱ ከሚገኙ የክፍል ደረጃዎች መካከል ለጥናቱ የተመረጠው ክፍል ሰባተኛ ነው፡፡ ትምህርት ቤቱንና የክፍል ደረጃውን በመምረጥ ረገድ አላማ ተኮር ናሙና (purposive Sampling) ተግባራዊ ተደርጓሌ፡፡ በጥናቱ ተሳታፊ የሆኑት ተማሪዎች በጠቅላይ ናሙና (Comprehensive Sampling) የተመረጡ ሲሆን በዘህም በክፍል ደረጃው የሚማሩ ሁሉም ተማሪዎች (ሰባቱም) በጥናቱ ተካተዋል፡፡ እነዘህ ተማሪዎች በቀጥታ በጥናቱ እንዲሳተፉ የተደረገበት ዋናው ምክንያት ቁጥራቸው ውስንና ከተጠቀሰው በላይ ባለመሆኑ ነው፡፡ለጥናቱ በመረጃ መስብሰቢያ ዘዴነት ተግባር ላይ የዋሉት ፈተና፣ የጽሑፍ መጠይቅና የተማሪዎች የቡድን ተኮር ውይይት ናቸው፡፡ ፈተናው ቅድመና ድህረ ትምህርት ፈተና ሲሆን ዋነኛ አላማውም ተጠኚ ተማሪዎች በመስተጋብራዊ የማስተማሪያ ዘዴ ከመማራቸው በፈትና በኋላ የነበራቸው የመጻፍ ክሂል ትምህርት የመማር ፍላጎት ምን ያህል ጉልህ ልዩነት እንዳሳየ ማረጋገጥ ነው፡፡ ሌላኛው የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴ ሆኖ ያገለገለው የቡዴን ተኮር ውይይት ሲሆን አላማው ደግሞ በፈተናና በጽሁፍ መጠይቅ ለተሰበሰቡት መረጃዎች ማጠናከሪያ ሀሳብ ማስገኘት ነው፡፡ በዚህም መሰረት የመጻፍ ክሂል ፈተናውና የጽሁፍ መጠይቁ በቅድመና ድህረ ትምህርት ትግበራው ላይ ለተጠኚዎች ቀርበው መረጃ የተሰበሰበባቸው ሲሆን የተገኘው ውጤትም በጥንድ ናሙና ቲ- ቴስት (Paird sample t-test) መጠናዊ የመረጃ መተንተኛ ስሌት ተሰሌቶ ( P< 0.05) የሆነ የጉልህነት መለያ ውጤት ተገኝቷል፡፡ በአንጻሩ በቡድን ተኮር ውይይቱ የተሰበሰበው መረጃም በአይነታዊ የመረጃ መተንተኛ ዘዴ ተተንትኖ በፈተናውና በጽሁፍ መጠይቁ የተገኘውን የሚደግፍ ውጤት አስገኝቷል ፡፡ በአጠቃላይ በሶስቱ የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴዎች ተሰብስበው ከተተነተኑት መረጃዎች የተገኘው ውጤት የሚያመለክተው መስተጋብራዊ የማስተማሪያ ዘዴ መስማት በተሳናቸው ተማሪዎች የመጻፍ ክሂል ችሎታና የመማር ፍላጎት ላይ የሚያሳድረው ተጽእኖ መኖሩንና ተጽዕኖውም አዎንታዊ መሆኑን ነው፡፡Item በቴክስት ውቅር ብልሃቶች በዐማርኛ ማንበብን መማር በተማሪዎች የአንብቦ መረዳት ችሎታ ላይ ያለው ተጽዕኖ- በስድስተኛ ክፍል ተተኳሪነት(አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ, 2009) እንድሪስ ዓባይ ደሊሉ; ዶ/ር ማረው ዓለሙየጥናቱ ዋና ዓላማ በቴክስት ውቅር ብልሃቶች ማንበብን መማር በተማሪዎች የማንበብ ተነሳሽነት፣ የማንበብ ግለብቃት እምነት፣ የማንበብ ትኩረትና የአንብቦ መረዳት ችሎታ ላይ ያለውን ቀጥተኛና ኢቀጥተኛ ተጽዕኖ መፈተሽ ነው፡፡ ዓላማውን ለማሳካትም መጠናዊ ምርምር ብሎም ፍትነትመሰል የጥናት ንድፍ ተግባራዊ ሆኗል፡፡ በመሆኑም በቴክስት ውቅር ብልሃቶች፣በብልሃትአልባ የቴክስት ውቅር እውቀትና አዘውትሮ በስራ ላይ በሚውለው የማንበብ ትምህርት አቀራረቦች ሦስት ቡድኖች ተለያይተው የአንብቦ መረዳት ትምህርትን በ12 ሳምንታት ለ24 ክፍለጊዜያት እንዲማሩ ተደርጓል፡፡ የጥናቱ ተሳታፊዎችም በደሴ ከተማ በአዲስፋና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርትቤት በ2009 ዓ.ም በመማር ላይ ከሚገኙ አራት የስድስተኛ ክፍል መማሪያ ክፍሎች ውስጥ በተራ እጣ ንሞና ዘዴ የተመረጡ ሦስት መማሪያ ክፍሎች ማለትም በብልሃት ቡድኑ 44፣ በብልሃትአልባ ቡድኑ 45፣ በቁጥጥር ቡድኑ 46 በጥቅሉ 135 ተማሪዎች ናቸው፡፡ ከተሳታፊዎቹም ቅድመትምህርትና ድህረትምህርት የአንብቦ መረዳት ውጤት፣ የማንበብ ትኩረት፣ የማንበብ ተነሳሽነትና የማንበብ ግለብቃት እምነት በፈተናዎችና በመጠይቆች አማካይነት መረጃዎች ተሰብስበዋል፡፡ መረጃዎቹም በአማካይ ውጤት፣ በመደበኛ ልይይት፣በአበርልይይት ብሎም የድኅረት ስሌት መሰረት ባለው የHayes (2013) ፕሮሰስ ፕላግኢን ኤስ.ፒኤስ.ኤስ (Hayes PROCESS plugin SPSS) ባለትይዩ የደንጋጊ ተላውጦዎች ትንተና ሞዴል 4 ተሰልተው ተተንትነዋል፡፡ የጥናቱ ግኝቶች እንዳመላከቱትም በሌሎቹ ሁለት አቀራረቦች ከተማሩት ተማሪዎች ይልቅ በቴክስት ውቅር ብልሃቶች ማንበብን የተማሩት በአንብቦ መረዳት ውጤታቸው፣ በማንበብ ተነሳሽነታቸው፣ በማንበብ ግለብቃት እምነታቸውና በማንበብ ትኩረታቸው ጉልህ መሻሻል አሳይተዋል፡፡ እንዲሁም የቴክስት ውቅር ብልሃቶች ትምህርት በአንብቦ መረዳት ውጤት ላይ ለሚያሳድረው ተጽዕኖ የማንበብ ትኩረትና የማንበብ ተነሳሽነት ከፊል የደንጋጊነት ሚና ሲያሳዩ የማንበብ ግለብቃት እምነት ግን ደንጋጊነቱ ጉልህ ሆኖ አልተገኘም፡፡ ከጥናቱ ግኝቶች በመነሳትም በቴክስት ውቅር ብልሃቶች ማንበብን መማር የተማሪዎችን የአንብቦ መረዳት ውጤት፣ የማንበብ ተነሳሽነት፣ የማንበብ ግለብቃት እምነትና የማንበብ ትኩረት ያሻሽላል ወደሚል ድምዳሜ ተደርሷል፡፡ ከዚህም ሌላ የቴክስት ውቅር ብልሃቶች ትምህርት በተማሪዎች የማንበብ ትኩረትና የማንበብ ተነሳሽነት ላይ የሚያስከትለው መሻሻል ኢቀጥተኛ በሆነ መንገድም የአንብቦ መረዳት ውጤት ከፍ እንዲል ያደርጋል ወደሚል መደምደሚያ ተደርሷል፡፡ ከጥናቱ ግኝቶች በመነሳትም ስነትምህርታዊ የመፍትሄ ሀሳቦች ተጠቁመዋል፤ የወደፊት የምርምር አቅጣጫዎችም ተመላክተዋል፡፡