Amharic Language, Literature and Folklore
Permanent URI for this collection
Browse
Recent Submissions
Item ሇኢትዮጵያ ሥነ ጽሐፍ የፍሌስፍና ድክትሬት ዱግሪ ማሟያ የቀረበ ጥናት(Addis Ababa University, 2024-03-02) በቴዎዴሮስ ገብሬ; ዮናስ አዴማሱአዲም በዖመናዊው የአማርኛ ሥነ ጽሐፍ ውስጥ የራሱን “የኪነት ሌማዴ” ሇመፍጠር የቻሇ ዯራሲ ሲሆን፣ ሚቶልጂው ከዘሁ ሌማዴ የሚመነጭ ይሆናሌ፡፡ የአዲም ሚቶች ከአንደ ሌብ ወሇዴ ወዯ ላሊው የሚዙመቱበት ጥብቅ ኪናዊ ሥርዒት አሊቸው፡፡ ይህ ሥርዒት አንዴም በትሌም ተከታታይነት፣ አንዴም በኀሌዮትና በርእዮት ተሸጋጋሪነት ሊይ የተመሠረተ ሲሆን፤ ክትትልቹና ሽግግሮቹ የሚመሩት ቋሚ በሆኑ ትእምርቶች እና ተስፋፊ ዖይቤዎች ነው፡፡ የአዲምን ሚታዊነት ጥቅሌ በሆነ እይታ በሁሇት መፈረጅ እንችሊሇን፡፡ በመጀመሪያው ፈርጅ ከባህለ በቀዲቸው አሌያም በውሰት ባመጣቸው ነባር ሚታዊ ትረካዎች ይገሇገሊሌ፡፡ በሁሇተኛው ፈርጅ በነባሩ የሚት ሌማዴ አምሳያ “ዖመናዊ” ሚትንና ሚታዊ መታገጊያን ይፈጥራሌ፡፡ ዲሩ ግን የፈጠራቸውንም ይሁን በውሰት አምጥቶ የተገሇገሇባቸውን ሚቶች በአመዙኙ በገዙ ራሱ ባህሌ አገረሰባዊ ኪኖችና ጽንሰ ሏሳቦች ሇመግራትና ሇማሰሌጠን መሞከሩ የሌብ ወሇድቹ መሇያ ባሔርይ ነው፡፡ የአዲም “ሚቶልጂ” ሲባሌ አንዴም ሌብ ወሇድቹ የተከየኑበትን ቋንቋ ሚታዊነት ሇማመሌከትም ይሆናሌ፡፡ ከዘህ ምርምር አጠቃሊይ መንፈስ የሚሰርጸው የአዲም “ሚቶልጂ” ዒቢይ አንዴምታ “ሚቶስ” ከ “ልጎስ” ጋር ያወረዯውን ዔርቅና የፈጸመውን ዲግማዊ ጋብቻ ያጠይቃሌ፡፡ አዲም ሌብ ወሇድቹን ሇመከየን ከተገሇገሇባቸው ስሌቶች መካከሌ ዒቢዩ ሚታዊ ኅሌዮ ነው፡፡ ሚታዊ ኀሌዮ በአዲም ሌማዴ ውስጥ ጽንሰ ሏሳቦችና ንዴፈ ሏሳቦች ከሌዩ ሌዩ ዱሲፕሉኖች የሚመሇመለበት፣ ከሳይንሳዊ ኀሌዮት ወዯ ኪናዊ እሴትነት የሚሸጋገሩበት ከማሔላት ተነስቶ የስንብት ቀሇማትን የዖሇቀ እጅግ ጠንካራ ስሌት ነው፡፡ አዲም ሚታዊ ኀሌዮውን የሚያዯራበት፣ የሚያፍታታበትና ሥግው የሚያዯርግበት ሌዩ ሌዩ መባያ ጉዲዮች እና/ወይንም የማስተማሰያ-የመፈከሪያ ዏውድች አለት፡፡ በዘህ ጥናት እንዯተረጋገጠው ከመባያዎቹና ከዏውድቹ መካከሌ “ሥፍራ”፣ “አካሌ” እና “ምግብ” ዏውራዎቹ ናቸው፡፡ የዘህ ጥናት ዒቢይ ዒሊማ በአዲም ሌብ ወሇድች ውስጥ ሚቶልጂን አጠቃሊይ ፍሬም በማዴረግ ሥፍራ፣ ምግብና አካሌ አንዴም ከተፈጥሮ ክስተትነት፣ አንዴም ከሳይንሳዊ ግኝትነት ወዯ ኪናዊ እሴትነት የሚሸጋገሩበትን ስሌት መተንተን ነው፡፡ በዘህ ሥር በአንዴ በኩሌ ሚታዊ ኀሌዮውን ሥግው ያዯረገባቸው ዏውራ የመባያ ጉዲዮችና የመፈከሪያ ዏውድች የአቀራረጽ ስሌትና ተጠየቅ ተመርምረዋሌ፡፡ መባያዎች ከራሳቸው ሊሇፉ ጉዲዮች መፈከሪያነት የሚያገሇግለ ትእምርቶች በመሆናቸው፣ በዘህ ጥናት ሥፍራን፣ አካሌንና ምግብን በመተርጎም ተጨማሪ ጭብጦችን ሇማዛመር ተችሎሌ፡፡ ዖመናዊው ዯራሲ፣ አዲም ረታ “ከጥንታዊው” ዒሇም በተቀዲ ተረክና የአስተሳሰብ ዖይቤ ታግዜ ሌብ ወሇድቹን ይከይን ዖንዴ በምን ዒይነት ነገረ ኪናዊ፣ ርእዮተ ዒሇማዊና ሥነ ሌቡናዊ ምክንያቶች እንዯተገፋፋ እና/ወይንም እንዯተገዯዯ ሇመመሇስ ተሞክሯሌ፡፡ ጥናቱ ከዘህ ባሇፈ ዖመናዊዎቹ ሌብ ወሇድች የፈጠሯቸውንም ይሁን በውሰት አምጥተው የተገሇገለባቸውን ሚቶች ሇመግራትና ሇማስሊት የታገባቸው ዒበይት አገረ ሰባዊ ኪኖችና ጽንሰ ሏሳቦች ምን እንዯሚመስለ የመመርመር ሚናም አሇው፡፡Item በአማርኛ ቋንቋ ትምህርት በይዘት ተኮር ዘዴ ሰዋስውን ማስተማር የሰዋስው እውቀትን ለማዳበር ያለው ፊይዳ(Addis Ababa University, 2024-01-02) አሸናፉ ደበበ; Masfiin Wadaajooየዙህ ጥናት ዋና ዓሊማ በአማርኛ ቋንቋ ትምህርት በይዘት ተኮር ዘዴ ሰዋስውን ማስተማር የሰዋስው እውቀትን ለመጨመር ያለው ፊይዲ ምን ያህሌ እንዯሆነ መፇተሸ ነው፡፡ ይህን ዓሊማ ሇመሳካት ጥናቱ ፍትነት መሰሌ ቅዴመና ዴሕረትምህርት ባሇቁጥጥር ቡዴን ንዴፍን ተከትሎሌ፡፡ ሇዙህም የቃሉቲ ሁሇተኛ ዯረጃ ትምህርት ቤትና የክፍሌ ዯረጃው (አስረኛ ክፍሌን) በአመቺ የንሞና ዘዳ፣ ሁሇት መማሪያ ክፍልችን (10B እና 10E) በቀሊሌ የእጣ ንሞና ስሌት እንዱሁም በመማሪያ ክፍልቹ የሚማሩ 95 ተማሪዎች በጠቅሊይ የንሞና ስሌት በጥናቱ ተሳታፉነት ተመርጠዋሌ፡፡ ከ95 ተማሪዎች መረጃ የተሰበሰበው በቅዴመና ዴሕረትምህርት የሰዋስው እውቀት መሇኪያ ፇተና ነው፡፡ አስተማማኝነቱን ሇመፇተሽም በዋናው ጥናት ባሌተሳተፈ ከ25 ተማሪዎች መረጃ ተሰብስቦ የተገኘው መረጃ በክሮንባኽ አሌፊ ተሰሌቶ ውጤቱን ከ0.7 በሊይ በመሆኑ ሇመረጃ መሰብሰቢያነት አገሌግሎሌ፡፡ በቅዴመትምህርት ፇተናው የተገኘው ውጤት በቁጥጥርና በሙከራ ቡዴን ተማሪዎች አማካይ ውጤት መካከሌ ጉሌህ የሆነ ስታትስቲካዊ ሌዩነት ባሇማሳየቱ ፍትነቱ ተካሂዶሌ፡፡ ከፍትነት በኋሊ ተጠኚ ተማሪዎች የዴህረትምህርት ፇተናውን ተፇትነዋሌ፡፡ በፇተናው ያስመገቡት አማካይ ውጤት የቁጥጥር ቡዴን 12.563፣ የሙከራ ቡዴን 14.404 ነው፡፡ በሁሇቱ ቡዴኖች አማካይ ውጤቶች መካከሌ ያሇው ሌዩነት ስታተስቲካዊ ጉሌህ መሆኑን ሇመፇተሽ በተዯረገው የነጻ ናሙና ቲቴስት ፍተሻ በተገኘው ውጤት መሰረት (t(93) = -3.462, P = 0.001) በቡዴኖቹ መካከሌ ጉሌህ ሌዩነት መኖሩን አሳይቷሌ። በመሆኑም ይት ተኮር የሰዋስው ትምህርት የሰዋስው እውቀትን የመጨመር ፊይዲ እንዲሇው መረዲት ተችሎሌ፡፡ ማስተማሪያ ዳው የሰዋስው እውቀትን ከመጨመር አንጻር ያሇውን የተጽዕኖ መጠን ሇመፇተሽ በተዯረገው የኮህን ዱ ፍተሻ ከፍተኛ ተጽዕኖ (d = 0.71) እንዲሇው ማረጋገጥ ተችሎሌ፡፡ ከጥናቱ ውጤት በመነሳት መምህራን የተማሪዎችን የሰዋስው እውቀት ሇማዲበር ይት ተኮር ዳን ቢተገብሩ፣ በሥርዓተ ትምህርት ዜግጅት ወይም ማሻሻሌ ሊይ የሚሰሩ ባሇሙያዎች የሰዋስው ትምህርትን አቀራረብና ማስተማሪያ ዳ ሲያጋጁ ሇይት ተኮር ዳ ትግበራ ምቹ የሆኑ አቀራረቦችንና ማስተማሪያ ዳዎችን ቢያካትቱ፣ በሰዋስው ማስተማሪያ ዳዎች ሊይ ምርምር ማዴረግ የሚፇሌጉ ተመራማሪዎች አማርኛን እንዯሁሇተኛ ቋንቋ በሚማሩ ተማሪዎች ሊይ ምርምር ቢያዯርጉ የሚለ የጥናት ጥቆማና አስተያየቶች በአጥኚው ቀርበዋሌ፡፡Item የመኤኒት ብሔረሰብ ሚት ማኅበረሰባዊ ፋይዳ(Addis Ababa University, 2014-06-23) አንዱዓለም አባተ; ዘሪሁን አስፋዉ (ተባባሪ ፕሮፌሰር)የመኤኒት ብሔረሰብ በዯቡብ ክሌሌ፣ በቤንች ማጂ ዝን ውስጥ የሚገኝ ብሔረሰብ ነው፡፡ የብሔረሰቡ አባሊት በዋናነት በመኤኒት ጎሌዱያ እና በመኤኒት ሻሻ ወረዲዎች ሲገኙ፣ በጥቂቱም ቢሆን በጉራ ፇርዲ እና በአንዲንዴ አጎራባች ወረዲዎች ውስጥ ይኖራለ፡፡ የመኤኒት ብሔረሰብን ታሪክ፣ ባሕሌና እሴቶችን ሇመረዲት ይህ ጥናት የብሔረሰቡ ሚትና ፊይዲ ያተኩራሌ፡፡ ሚትን አስመሌክቶ በብሔረሰቡ ሊይ የተጠኑ ጥቶች አሇመኖራቸው ይሄንን ጥናት ሇማዴረግ ዏቢይ ምክንያት ሲሆን፣ ጥናቱን የተሳካ እንዱሆንም መረጃዎች በቀዲማይ እና በካሌአይ የመረጃ ምንጮች ተሰብስበዋሌ፡፡ የተሰበሰቡት መረጃዎች በተረካዊ እና በመዋቅራዊ ንዴፇ ሀሳቦች ተተንትነዋሌ፡፡ ይህ ጥናት ዋና ዋና የመኤኒት ብሔረሰብ ሚቶችን ሇይቷሌ፡፡ እነሱም የአፇጣጠር ሚት፣ የመንፇሳዊ ሚት፣ የመስተጋዴሊውያን ሚትና የዲግም ውሌዯት ሚት ናቸው፡፡ በጥናቱ በየሚቶቹ ውስጥ የሚገኙ ትዕምርቶች በትንተናው ወቅት ተፇክረዋሌ፡፡ የብሔረሰቡ አባሊት ሇሚቶቹ ያሊቸው አመሇካከትም ተብራርቷሌ፡፡ እነዙህ ሚቶችም ሇብሔረሰቡ የሚሰጧቸው ሌዩ ሌዩ ፊይዲዎችም እንዱሁ በጥናቱ ግኝት ውስጥ ቀርበዋሌ፡፡ የብሔረሰቡ አባሊት ሇሚያነሷቸው ሇዒሇማዊ ጥያቄዎች መሌስ በመስጠት የብሔረሰቡ ሚቶች የብሔረሰቡን ሌዩ ሌዩ ባሕልች፣ ታሪኮች፣ ሃይማኖትን እና ዕሴቶች የመግሇጥ፣ የማስተማር፣ የመግታትና የመቆጣጠር፣ ማኅበረሰባዊ መዋቅርን የመገንባት፣ የሥሌጣን ክፌፌሌ እንዱኖር የማዴረግ፣ የተሇያዩ የኅብተረሰብ ክፌልችን አንዴ የማዴረግ ፊይዲዎች እንዲሊቸው በጥናቱ ተመሌክቷሌ፡፡ ይህ በመኤኒት ብሔረሰብ ሚት ፊይዲ ሊይ ያተኮረው ጥናት ብሔረሰቡ ፀንቶ የቆመባቸውን እና የቡዴን ሕሊዌውን ያስጠበቀባቸው መሠረቶች አሳይቷሌ፡፡ የመኤኒት ብሔረሰብ ሚቶች እንዱጠበቁ፣ እንዱዲብሩ በሌማትና ዕዴገት ሊይ የሊቀ ሚና እንዱኖራቸው የሚመሇከታቸው አካሊት ዴጋፌ እንዱያዯርጉ የይሁንታ ሀሳብ በማቅረብ ጥናቱ ተጠናቋሌ፡፡Item በአማርኛ ቋንቋ ትምህርት በይት ተኮር ዳ ሰዋስውን ማስተማር የሰዋስው እውቀትን ሇማዲበር ያሇው ፊይዲ ፌተሻ(Addis Ababa University, 2017-06-01) አሸናፉ ደበበ; ሙለሰው አስራቴ (ድ/ር)የዙህ ጥናት ዋና ዓሊማ በአማርኛ ቋንቋ ትምህርት በይት ተኮር ዳ ሰዋስውን ማስተማር የሰዋስው እውቀትን ሇመጨመር ያሇው ፊይዲ ምን ያህሌ እንዯሆነ መፇተሸ ነው፡፡ ይህን ዓሊማ ሇመሳካት ጥናቱ ፍትነት መሰሌ ቅዴመና ዴሕረትምህርት ባሇቁጥጥር ቡዴን ንዴፍን ተከትሎሌ፡፡ ሇዙህም የቃሉቲ ሁሇተኛ ዯረጃ ትምህርት ቤትና የክፍሌ ዯረጃው (አስረኛ ክፍሌን) በአመቺ የንሞና ዳ፣ ሁሇት መማሪያ ክፍልችን (10B እና 10E) በቀሊሌ የእጣ ንሞና ስሌት እንዱሁም በመማሪያ ክፍልቹ የሚማሩ 95 ተማሪዎች በጠቅሊይ የንሞና ስሌት በጥናቱ ተሳታፉነት ተመርጠዋሌ፡፡ ከ95 ተማሪዎች መረጃ የተሰበሰበው በቅዴመና ዴሕረትምህርት የሰዋስው እውቀት መሇኪያ ፇተና ነው፡፡ አስተማማኝነቱን ሇመፇተሽም በዋናው ጥናት ባሌተሳተፈ ከ25 ተማሪዎች መረጃ ተሰብስቦ የተገኘው መረጃ በክሮንባኽ አሌፊ ተሰሌቶ ውጤቱን ከ0.7 በሊይ በመሆኑ ሇመረጃ መሰብሰቢያነት አገሌግሎሌ፡፡ በቅዴመትምህርት ፇተናው የተገኘው ውጤት በቁጥጥርና በሙከራ ቡዴን ተማሪዎች አማካይ ውጤት መካከሌ ጉሌህ የሆነ ስታትስቲካዊ ሌዩነት ባሇማሳየቱ ፍትነቱ ተካሂዶሌ፡፡ ከፍትነት በኋሊ ተጠኚ ተማሪዎች የዴህረትምህርት ፇተናውን ተፇትነዋሌ፡፡ በፇተናው ያስመገቡት አማካይ ውጤት የቁጥጥር ቡዴን 12.563፣ የሙከራ ቡዴን 14.404 ነው፡፡ በሁሇቱ ቡዴኖች አማካይ ውጤቶች መካከሌ ያሇው ሌዩነት ስታተስቲካዊ ጉሌህ መሆኑን ሇመፇተሽ በተዯረገው የነጻ ናሙና ቲቴስት ፍተሻ በተገኘው ውጤት መሰረት (t(93) = -3.462, P = 0.001) በቡዴኖቹ መካከሌ ጉሌህ ሌዩነት መኖሩን አሳይቷሌ። በመሆኑም ይት ተኮር የሰዋስው ትምህርት የሰዋስው እውቀትን የመጨመር ፊይዲ እንዲሇው መረዲት ተችሎሌ፡፡ ማስተማሪያ ዳው የሰዋስው እውቀትን ከመጨመር አንጻር ያሇውን የተጽዕኖ መጠን ሇመፇተሽ በተዯረገው የኮህን ዱ ፍተሻ ከፍተኛ ተጽዕኖ (d = 0.71) እንዲሇው ማረጋገጥ ተችሎሌ፡፡ ከጥናቱ ውጤት በመነሳት መምህራን የተማሪዎችን የሰዋስው እውቀት ሇማዲበር ይት ተኮር ዳን ቢተገብሩ፣ በሥርዓተ ትምህርት ዜግጅት ወይም ማሻሻሌ ሊይ የሚሰሩ ባሇሙያዎች የሰዋስው ትምህርትን አቀራረብና ማስተማሪያ ዳ ሲያጋጁ ሇይት ተኮር ዳ ትግበራ ምቹ የሆኑ አቀራረቦችንና ማስተማሪያ ዳዎችን ቢያካትቱ፣ በሰዋስው ማስተማሪያ ዳዎች ሊይ ምርምር ማዴረግ የሚፇሌጉ ተመራማሪዎች አማርኛን እንዯሁሇተኛ ቋንቋ በሚማሩ ተማሪዎች ሊይ ምርምር ቢያዯርጉ የሚለ የጥናት ጥቆማና አስተያየቶች በአጥኚው ቀርበዋሌ፡፡Item የክቡር ዶክተር ሀዲስ ዓለማየሁ የሕይወት ታሪክና የስነፅሑፍ ስራዎቻቸው(አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 1992) ፈለቀች እሸቴ; ዘሪሁን አስፋውየክቡር ዶክተር ሀዲስ ዓለማየሁ የሕይወት ታሪክItem የአርጐባ ብሄረሰብ የወሊድ፣ የጋብቻና የሀዘን ስነ ስርዓቶች ክዋኔ ትንተና፤ በአፋር ክልል፣ ዞን ሶስት፣ አርጐባ ልዩ ወረዳ(2017-08-16) እታገኘሁ አስረስ; ዘሪሁን አስፋው (ተባባሪ ኘሮፌሰር)የፎክሎር አንድ ክፍል የሆነው ሀገረሰባዊ ልማድ ከሚይዛቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ ስነ ስርዓት (Ritual) ነው፡፡ ከስነ ስርዓት ዓይነቶች መካከል ደግሞ የህይወት ሽግግር ስነ ስርዓቶች ይገኛሉ፡፡ ይህ ጥናት በህይወት ሽግግር ስነ ስርዓቶች ላይ ትኩረት ያደረገ ሲሆን "የአርጐባ ብሄረሰብ የወሊድ፣ የጋብቻና የሀዘን ስነ ስርዓቶች ክዋኔ ትንተና፤ በአፋር ክልል፣ ዞን ሶስት፣ አርጐባ ልዩ ወረዳ" በሚል ርዕስ የቀረበ ነው፡፡ የጥናቱ ዋና ዓላማ በአፋር ክልል ከሚኖረው የአርጐባ ብሄረሰብ የህይወት ሽግግር ስነ ስርዓቶች መካከል የወሊድ፣ የጋብቻና የሀዘን ስነ ስርዓቶችን ክዋኔ መተንተን ነው፡፡ በአፋር ክልል የሚኖረውን የአርጐባ ብሄረሰብ የወሊድ፣ የጋብቻና የሀዘን ስነ ስርዓቶች ለመተንተን የክዋኔ፣ መዋቅራዊ፣ ትዕምርታዊና ተግባራዊ ንድፈ ሀሳቦች ጥቅም ላይ የዋሉ ሲሆን የጥናቱን ዓላማ ለማሳካትና የምርምር ጥያቄዎችን ለመመለስ ካልዓይና ቀዳማይ መረጃዎች ተሰብስበዋል፡፡ ካልዓይ መረጃ ከጽሁፍ ሰነዶች፣ ቀዳማይ መረጃ ደግሞ የመስክ ስራ በማከናወን የተሰበሰበ ሲሆን በመስክ መረጃን ለመሰብሰብ ጥቅም ላይ የዋሉ ምልከታ፣ ቃለመጠይቅና ቡድን ተኮር ውይይት ዘዴዎች ናቸው፡፡ የጥናት ቦታና የመረጃ ሰጪ መረጣ የተከናወነው በአላማ ተኮርና በጠቋሚ የንሞና ዘዴ ነው፡፡ መረጃ የተሰበሰበባቸው አውዶች ተፈጥሯዊና አርቴፊሻል አውዶች ሲሆኑ መረጃው ከዓይነታዊ የመረጃ መተንተኛ ዘዴዎች ውስጥ ኢትኖግራፊ የጥናት ሞዴልን በመጠቀም ተተንትኗል፡፡ የሜታ ፎክሎር ምርመራም በመረጃ መተንተኛነት ጥቅም ላይ ውሏል፡፡ የጥናቱ ግኝት እንደሚያሳየው በአፋር ክልል የሚኖረው የአርጐባ ብሄረሰብ የጋብቻ ስነ ስርዓት ክዋኔ መዋቅር በቅድመ መለየት፣ መለየት፣ ሽግግርና መቀላቀል ደረጃዎች ሊከፈል የሚችል ሲሆን የወሊድና የሀዘን ስነ ስርዓቶች ክዋኔዎች ደግሞ በመለየት፣ ሽግግርና መቀላቀል ደረጃዎች ሊከፈሉ የሚችሉ ናቸው፡፡ በብሄረሰቡ የወሊድ ስነ ስርዓት ክዋኔ ስነቃል (ዱዓዎች፣ ዝኪሮች)፣ ቁሳዊ ባህል (ሽታ፣ አዝጋሮ፣ ወይባ፣ አልባሳት) እና ሀገረሰባዊ ልማድ (እምነቶች፣ ባህላዊ ሕክምና፣ ጭስ መሞቅ) ፎክሎሮች ተለይተዋል፡፡ በጋብቻ ስነ ስርዓት ክዋኔ ስነቃል (ቃል ማሰሪያዎች፣ መወከያዎች፣ ዱዓዎች)፣ ቁሳዊ ባህል (ወይደል፣ ምግብና መጠጥ፣ አልባሳት፣ ጌጣጌጥ፣ ጉፍታ)፣ ሀገረሰባዊ ልማድ (እምነቶች፣ ጭስ መሞቅ) እና ሀገረሰባዊ ትውን ጥበባት (ሺሎ፣ ዘፈኖች) ፎክሎሮች ተለይተዋል፡፡ በሀዘን ስነ ስርዓት ክዋኔም ስነቃል (ዱዓ፣ ማጽናኛዎች፣ መሰናበቻዎች)፣ ቁሳዊ ባህል (ምግብና መጠጥ፣ የከፈን ጨርቅ፣ ማግ፣ መዋስ) እና ሀገረሰባዊ ልማድ (ባህላዊ ህክምና፣ እምነት) ፎክሎሮች ተለይተዋል፡፡ በብሄረሰቡ በወሊድ ስነ ስርዓት ክዋኔ ውስጥ ያሉ ቃላዊ (የዱዓ ቃላት)፣ ቁሳዊና (ማር) ድርጊታዊ (ጣትን በገበታ ዙሪያ ማድረግ፣ ገበታን ከፍ ማድረግ፣ ድፍን ቅል አልጋ ላይ ማድረግ)፣ በጋብቻ ስነ ስርዓት ክዋኔ ውስጥ ያሉ ቃላዊ (የዱዓ ቃላት)፣ ቁሳዊ (የወይደል ቀለም፣ ጉፍታ) እና ድርጊታዊ (ለሙሽራ ጉፍታ የምትጭን ሴት አግብታ ያልፈታች መሆኗ) እና በሀዘን ስነ ስርዓት ክዋኔ ውስጥ ያሉ ድርጊታዊና (ጥልፍ መተርተር፣ ውሀ ማርከፍከፍና እርጥብ ቅጠል መጐዝጐዝ፣ መዋስን በጠዋት ውሀ አርከፍክፎ ማጠፍ፣ እጅንና ፊትን በቀዝቃዛ ውሃ መታጠብ) ቁሳዊ (ውሀ፣ መዋስ) ትዕምርቶች ተለይተዋል፡፡ የብሄረሰቡ የወሊድ ስነ ስርዓት ማህበራዊና (ወላድ መንከባከብ፣ አራስ መጠየቅ) ስነ ልቡናዊ (ባህላዊ ህክምናና የአምሮት ስነ ስርዓት) ፋይዳዎች አሉት፡፡ የብሄረሰቡ የጋብቻ ስነ ስርዓት የአሻጋሪነት (ትዳር የሌለውን ሰው ወደ ባለትዳርነት)፣ ማህበራዊ (ሰዎችን በአንድ ያገናኛል)፣ ኢኮኖሚያዊ (ስጦታዎች)፣ ስነ ልቡናዊና (ዱዓና ባዷሼህ) የተግባቦትና የማዝናናት (ዘፈኖች) ፋይዳዎች አሉት፡፡ የብሄረሰቡ የሀዘን ስነ ስርዓት ተግባቦታዊና ማህበራዊ (ለቅሶ መድረስ)፣ ኢኰኖሚያዊና (ሀፈሻ) ስነ ልቡናዊ (በጋራ ማልቀስና ሶደቃ) ፋይዳዎች አሉት፡፡ ለውጥን ተቋቁመው የቀጠሉ ክዋኔዎች ቢኖሩም በብሄረሰቡ የወሊድና የሀዘን ስነ ስርዓቶች ላይ የክዋኔ ለውጦች፤ በብሄረሰቡ የጋብቻ ስነ ስርዓት ላይ ደግሞ የክዋኔና የመዋቅር ለውጦች ታይተዋል፡፡ ምሳሌያዊ አነጋገሮች ተለይተው የሜታ ፎክሎር ምርመራም ተደርጐባቸዋል፡፡ በጋቸኔ ጤና ጣቢያ የተሰራው ባህላዊ ጐጆ ለታሰበለት ዓላማ ቢውል፣ የነፍሰጡር የምግብ ክልክሎችና ከነፍሰጡሯ ጤና አንፃር ጉዳት ያለው መሆኑና አለመሆኑ ቢጠና፣ በወሊድ ጊዜ የሚከወኑ አንዳንድ ክዋኔዎች ለምሳሌ፣ መነቅነቅ የሚያስከትሏቸው የጤና ጉዳቶች ካሉ በጥናት ቢለዩ፣ ሀፈሻን ከዘመናዊ የመረዳጃ ተቋማት ጋር ማስተሳሰር ቢቻል፣ ዚያራ በዝርዝር ቢጠና ጥሩ ነው፡፡Item የድጋፍ ብልሃቶች በአንብቦ የመረዳት ችሎታ እና ግለመር ማንበብ ላይ ተፅዕኖ፤ በ7ኛ ክፍል ተማሪዎች ተተኳሪነት(አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ, 2016) ራሔል ሲሳይ ተገኘ; ፕሮፌሰር ተስፋየ ሸዋየየዚህ ጥናት ዓላማ የድጋፍ ብልሃቶች የተማሪዎችን በአማርኛ ቋንቋ አንብቦ የመረዳት ችሎታ እና ግለመር ማንበብ ላይ ያላቸውን ተፅዕኖ መፈተሸ ነበር፡፡ ጥናቱ በዓይነቱ ቅደምተከተላው ቅይጥ (በአመዛኙ መጠናዊ) ሲሆን ቅድመና ድህረ ትምህርት በለቁጥጥር ቡድን ፍትነት ቡድን ፍትነት መሰል ንድፍን የተከተለ ነው፡፡ በ2015 ዓ.ም በአዲስአበባ ከተማ አስተዳደር፡ በጉለሌ ክፍለ ከተማ በአድስተስፋ አንደኛ ደረጃ ትምህርትቤት የ7ኛ ክፍል ተማሪዎች ተሳትፈዋል፡፡ መረጃዎችን ለመሰብሰብም አንብቦ የመረዳት ችሎታ ፈተናና የግለመር ማንበብ መጠይቅ ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡ ሌላው በአግዥነት ድህረቡድን ተኮር ውይይት ተግባራዊ ሆኗል ፡፡ እንዲሁም ሁለቱ ቡድኖች በተቀመጠላቸው የማስተማሪያ መንገድ መማርቸውን ለማረጋገጥ ሲባል ምልከታ ተካሂዷል ፡፡በቅድመ ፈተናና መቅድመ የጽሑፍ መጠይቅ የተገኙ ውጤቶች በጥንድና ነፃ ቲ-ትስቶች የትንተና ስልት እንዲሁም በድኀረ ፈተናና በድኀረ የጽሑፍ መጠይቅ የተገኙ ውጤቶች በጥንድ፡ ነፃ ቲ- ትስቶችና በአበር ልይይት ትንተና ስልቶች ተተንትነዋል፡፡ በተጨማሪም ከድህረቡድን ተኮር ውይይት የተገኙት ውጤቶችም እንደሚያመለክቱት በቅድመፈተናና በቅድመየጽሑፍ መጠይቅ ቡድኖች ተመጣጣኝ አማካይ ውጤቶች ያስመዘገቡ ሲሆን በድኀረ የጽሑፍ መጠይቅ ገለመር ማንበብ የሙከራ ቡድኑ ተማሪዎች ከቁጥጥት ቡድኑ ተማሪዎች ጉልህ የሆነ ልዩነት አሳይተዋል (P= <0.05):: ይህም ውጤት በድጋፍ ብልሀቶች መማር የተማሪዎችን አንብቦ የመረዳት ችሎታና ግለመር ማንበብን ከማሻሻል አኳያ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቁሟል፡፡ በተገኙት ውጤቶች በመመስረት የመፍትሄ ሀሳቦችና የጥናት ጥቆማዎች ተሰጥተዋል፡፡Item የስሜታዊ ብልህነት፣ የመጻፍ ችሎታና የመጻፍ ተነሳሽነት ፆታተኮር ተዛምዶ፤ በ11ኛ ክፍል ተማሪዎች ተተኳሪነት(አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ, 2016) በለጠ ሕሉፍ ኪሮስ; ፕሮፌሰር ጌታሁን አማረየጥናቱ ዋና ዓላማ የስሜታዊ ብልህነት፣ የመጻፍ ችሎታና የመጻፍ ተነሳሽነት ያላቸውን ተዛምዶ ከጾታ አንጻር መፈተሽ ነበር፡፡ ዓላማውን ለማሳካትም ጥናቱ በተለዋዋጮቹ መካከል ያለውን ዝምድና የማሳየት አላማ ስላለው የተከተለው ዲዛይን (ስልት) ተዛምዷዊ ነበር፡፡ የጥናቱ ተሳታፊዎች በ2013 ዓ.ም በደሴ ከተማ አስተዳደር የሁለተኛ ደረጃ የሁለተኛው ሳይክል ካላቸው ትምህርትቤቶች መካከል በመምህር አካለወልድ የነበሩ ከ11ኛ G እስከ L ክፍል የማኅበራዊ ሳይንስ (107 ወንዶችና 69 ሴቶች በአጠቃላይ 176) ተማሪዎች በቀላል የዕጣ ንሞና ዘዴ የተወሰዱ ናቸው፡፡ ከተሳታፊዎቹ፤ የስሜታዊ ብልህነት መጠይቅና የመጻፍ ተነሳሽነት መጠይቅ እንዲሞሉ እንዲሁም የመጻፍ ችሎታን ለመፈተሽ የሚያገለግል የመጻፊያ ርእስ በመስጠት እንዲጽፉ በማድረግ መረጃዎች ተሰብስበዋል፡፡ የተገኙት መረጃዎችም በገላጭ ስታትስቲክስ (በአማካይ ውጤትና በመደበኛ ልይይት)፣ የርስበርስና የጠራ ዝምድናቸውን ለመለየት በፒርሰን የተዛምዶ መለኪያ እንዲሁም በከፊል የተዛምዶ መፈተሻ ዘዴ ተሰልተው ተተንትነዋል፡፡ የጥናቱ ውጤቶች እንዳመላከቱትም በስሜታዊ ብልህነት፣ በመጻፍ ችሎታና በመጻፍ ተነሳሽነት መካከል ጾታተኮር ዝምድና ታይቷል፡፡ በሌላ በኩል የስሜታዊ ብልህነት ዘርፎች ከመጻፍ ችሎታ ጋር ተዛምዷቸው ከጾታ አንጻር ልዩነት አላቸው፡፡ እንዲሁም የስሜታዊ ብልህነትና የመጻፍ ችሎታ ከተነሳሽነት አንጻር ልዩነት አሳይተዋል፡፡ በመጻፍ ችሎታና በመጻፍ ተነሳሽነት መካከል ጾታን መሰረት አድርጎ ልዩነት አልታየም፡፡ ከጥናቱ ግኝቶች በመነሳትም ጾታ ጣልቃገብ ሲሆን በተላውጦዎቹ መካከል ልዩነት ያሳያል ወደሚልና የስሜት ብልህነትና የመጻፍ ችሎታ ተዛምዶ የሚኖራቸው የመጻፍ ተነሳሽነት ሲኖር ነው ወደሚል ድምዳሜ ተደርሷል፡፡ ከጥናቱ ግኝቶች በመነሳትም አስተያየቶች ተጠቁመዋል፤ የወደፊት የምርምር አቅጣጫዎችም ተመላክተዋል፡፡Item ፕሮጀክት ተኮር መማር፣ በመጻፍ ችሎታና ተነሳሽነት ላይ ያለው ተፅዕኖ፤ በ10ኛ ክፍል አማርኛ ቋንቋ አፍፈት ተማሪዎች ተተኳሪነት(አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ, 2016) በስመኝ አለምነህ; ጌታሁን አማረ (ፕ/ር); ግርማ ገብሬ (ዶ/ር)የዚህ ጥናት ዓላማ ፕሮጀክት ተኮር መማር፣ ለተማሪዎች የመጻፍ ችሎታእናተነሳሽነትመሻሻል ያለውን ሚና መፈተሽ ነው፡፡ ዓላማውን ከግብ ለማድረስምቅድመትምህርትናድኅረ ትምህርት ፈተና ባለቁጥጥር ቡድን ከፊል ሙከራዊ (quasi-expermental) ስልትተግባራዊ ሆኗል፡፡ በጥናቱ የትግበራ ሂደትም አማራ ክልል በአላማተኮርንሞናተመርጧል፤ ደብረማርቆስ ከተማ የሚገኘው ንጉስ ተክለሃይማኖትአጠቃላይሁለተኛደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ደግሞ በአመቺ ንሞና ከተመረጠበኋላ በዚህትምህርትቤት የሚገኙ የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች በዕጣ ተመርጠው ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ ክልሉበዓላማተኮር ንሞና የተመረጠው ጥናቱ አፍፈት ተማሪዎች ላይ የሚያተኩርበመሆኑነው።ትምህርት ቤቱ በአመቺ ንሞና የተመረጠበት ምክንያትምጥናቱከፊልፍትነታዊእንደመሆኑ መጠን ትምህርት ቤቱን እና የአማርኛ ቋንቋ መምህራንን ልዩትብብርእናድጋፍ የሚፈልጉ ጉዳዮችን የሚጠይቅ በመሆኑ ለዚህም የትምህርትቤቱአስተዳደር፣መምህራንና ተማሪዎች ለጥናቱ ፈቃደኛ በመሆናቸው ነው፡፡ የ10ኛ ክፍልተማሪዎችበዕጣየተመረጡበት ምክንያት ደግሞ ከ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በስተቀር ጥናቱበ9ኛ፣ 10ኛእና11ኛ ክፍል ተማሪዎች ላይ ቢካሄድ በተማሪዎች መረጃ የመሰብሰብሂደትላይችግርአይኖርም ተብሎ ስለታሰበ ነው፡፡ መረጃዎች ከተሳታፊ ተማሪዎችበመጻፍችሎታፈተናእና በመጻፍ ተነሳሽነት የጽሑፍ መጠይቅ ተሰብስበዋል፡፡ የተገኙትመረጃዎችምየመተንተኛ ስልቱ እሙኖች በገላጭ ስታቲስቲክስ ከተፈተሹ በኋላ በሙከራናበቁጥጥርቡድኖች መካከል ልዩነት መኖር አለመኖሩን ለመፈተሽ የቅድመና ድኅረትምህርትአጠቃላይ የመጻፍ ችሎታ፣ ንዑሳን ችሎታዎች (ይዘት፣ አደረጃጀት፣ የቃላትአመራረጥናአጠቃቀም፣ የቋንቋ አጠቃቀም እና ስርዓተ አጻጻፍ) አማካይ ውጤቶችና የመጻፍተነሳሽነትየጽሑፍ መጠይቅ አማካይ ውጤቶች በባለብዙ ተላውጦ ልይይትትንተናዘዴ(Multivariate Analysis of Variance, MANOVA) ተሰልተውተተንትነዋል፡፡ በተገኙትውጤቶች መሠረትም፣ የተማሪዎች አጠቃላይ የመጻፍ ችሎታእና ንዑሳንችሎታዎች(ይዘት፣ አደረጃጀት፣ የቃላት አመራረጥና አጠቃቀም፣ የቋንቋ አጠቃቀምእናስርዓተአጻጻፍ) እንዲሁም የመጻፍ ተነሳሽነት የጽሑፍ መጠይቅ ውጤቶችየሙከራቡድንተማሪዎች ከቁጥጥር ቡድን ተማሪዎች አማካይ ውጤቶች ተሽለውና ጉልህ (p<.05) ልዩነትያላቸው ሆነው ተገኝተዋል። በዚህም መሠረት ፕሮጀክት ተኮር መማርየተማሪዎችንአጠቃላይ የመጻፍ ችሎታ እና ንዑሳን ችሎታዎች እንዲሁም የመጻፍተነሳሽነትለማሻሻልሚና እንዳለውና ሚናውም ከፍተኛ እንደሆነ ጥናቱ አሳይቷል፡፡ በመሆኑም፣ የመጻፍትምህርትን በፕሮጀክት ተኮር መማር ተግባራት ማቅረብ እንደሚያስፈልግተጠቁሟል፡፡Item የአፍ መፍቻ ቋንቋን በትምህርት መስጫነት የመጠቀም አመለካከቶችና ተግዳሮቶች፤ በስልጤ፣ በሀድያ፣ በከምባታና በወላይታ ቋንቋዎች ተተኳሪነት(አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ, 2010) በጎሰው የሽዋስ መንግስት; ፕ/ር ባየ ይማምየጥናቱ ዋና ዓላማ የአፍ መፍቻ ቋንቋን በትምህርት መስጫነት በመጠቀም ረገድ እየታዩ ያሉ አመለካከቶችንና እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶችን ማጥናት ነው፡፡ ዓላማውን ለማሳካትም የጥናቱ ንድፍ ውህድ ዘዴን የተከተለ ሲሆን ከውህድ ጥናት ንድፍ ንኡስ ክፍሎችም ባለትይዩ አቻ ውህድ ዘዴ (convergent parallel mixed method) ተግባራዊ የተደረገበት ነው፡፡ ለጥናቱ አስተማማኝ መረጃዎችን ለማግኘትም ቅንጅታዊ የምርምር ዘዴ ተግባራዊ ተደርጓል፡፡ የጥናቱ ቦታም የደቡብ ኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልልን ሲሆን፣ በዚህ ክልል ውስጥ “medium MT exit model”ን (ከአንደኛ እስከ አራተኛ ክፍል) ከሚጠቀሙ ዞኖች መካከል ስልጤን፣ ወላይታን፣ ከምባታንና ሀድያን በእጣ ንሞና በመምረጥ በጽሁፍና በቃል መጠይቅ መረጃ ተሰብስቧል፡፡ በእነዚህ ዞኖች ውስጥም በ18 የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ በስምንት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ በሁለት የመምህራን ኮሌጆች፣ በስምንት የገጠርና የከተማ ቀበሌዎች፣ በ12 የዞንና የወረዳ ትምህርት መምሪያዎች ከወላጆች፣ ከመምህራን፣ ከተማሪዎች፣ ከትምህርት ባለሞያዎችና ሀላፊዎች መረጃ ተሰብስቧል፡፡ የተገኙ መረጃዎችም በየንዑስርዕሰ ጉዳዮች ስር ተደራጅተው በገላጭ የትንተና ስልት ተተንትነዋል፡፡ ትንተናውን ለማካሄድም የማህበራዊ ሳይንስ ጥናት መረጃዎችን ለመተንትን የተዘጋጀው የኮምፒተር ፕሮግራም SPSS /Statistical Package for the Social Science/ ጥቅም ላይ ውሏል፡፡ የጥናቱ ግኝቶች እንዳመለከቱትም አብዛኞቹ የጥናቱ ተተኳሪዎች የአንደኛ ደረጃ ትምህርት በአፍ መፍቻ ቋንቋ በመሰጠቱ ደስተኞች እንደሆኑና እንደሚደግፉ ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡ ከአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (ከአንደኛ እስከ አራተኛ ክፍል) ባለፈ ግን ለትምህርት መስጫነት ከአፍ መፍቻ ቋንቋ ይልቅ እንግሊዝኛን እንደሚመርጡ ለማወቅ ተችሏል፡፡ የአመለካከቶቹ መንስኤዎችም ባብዛኛው ኢኮኖሚያዊ፣ ስነትምህርታዊና ስነልቦናዊ ሆነው ተገኝተዋል፡፡ ሌላው የተግዳሮት ጉዳይ ሲሆን፣ በአፍ መፍቻ ቋንቋ በማስተማር ሂደት ላይ አብይ ተግዳሮት ሆኖ በዚህ ጥናት የተገኘው ስነትምህርታዊ ተግዳሮት ነው፡፡ የዚህም መንስኤው ባብዛኛው የፖለቲካ ቁርጠኝነት አለመኖር እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በመጨረሻም ከጥናቱ ግኝቶች በመነሳት አስተያየቶች ቀርበዋል፡፡ የወደፊት የምርምር አቅጣጫዎችም ተጠቁመዋል፡፡Item ትብብራዊ መማር የተማሪዎችን የመፃፍ ክሂል፣ ማህበራዊ ክሂልና የመፃፍ ተነሳሽነት ለማሳደግ ያለው ሚና (አማርኛን በሁለተኛ ቋንቋነት በሚማሩ በባሌ ዞን በዘይበላ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ7ኛ ክፍል ተማሪዎች ተተኳሪነት)(አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ, 2009) ግርማ ኃይሉ; ዶ/ር ጌታቸው እንዳላማውየጥናቱ ዓላማ ትብብራዊ መማር የተማሪዎችን የመፃፍ ክሂል፣ ማህበራዊ ክሂልና የመፃፍ ተነሳሽነት ለማሳደግ ያለውን ሚና መፈተሽ ነው፡፡ ጥናቱም የተከናወነው አማርኛን በሁለተኛ ቋንቋነት በሚማሩ በባሌ ዞን በዘይበላ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ7ኛ ክፍል ተማሪዎች ተተኳሪነት ነው፡፡ ጥናቱ ከፊል ፍትነታዊነት መሰል የምርምር (Quasi Experimental Research) ስልትን ተከትሏል፡፡ የመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያዎቹም ፈተና፣ የጽሑፍ መጠይቅና ቃለመጠይቅ ናቸው፡፡ የፈተናዎቹ ውጤት በt- ቴስት አማካይነት ተነጻጽሯል፡፡ ውጤቱንም ለማነጻጸር የስህተት ይሁንታ መጠኑ በ0.05 (5%) ባለሁለት ጫፍ ነው፡፡ ከዋናው ጥናት በፊት የቁጥጥር ቡድኑና የሙከራ ቡድኑ የነበራቸውን የቅድመሙከራ የመጻፍ ክሂል ችሎታ ከወዲሁ ለማወቅ የቅድመትምህርት ፈተና ተፈትነዋል፡፡ በቅድመትምህርት የፈተና ውጤታቸውም በአማካይ የቁጥጥር ቡድኑ 52.67 እንደዚሁም የሙከራ ቡድኑ 52.42 ሆኗል፡፡ ይህ ውጤት ሁለቱም ቡድኖች በድህረትምህርት ፈተና የመጻፍ ችሎታቸው ተቀራራቢ መሆኑን ጠቁሟል፡፡ በቀጣይ የቁጥጥር ቡድኑ በተለመደው መንገድ፣ የሙከራ ቡድኑ በትብብራዊ መማር ለአንድ ሴሚስተር ያህል ከተማሩ በኋላ ሁለቱም ቡድኖች የድህረትምህርት ፈተና ተፈተኑ፡፡ የተሳታፊዎቹ የድህረትምህርት ፈተና ውጤት በአማካይ የቁጥጥር ቡድኑ 53.13፣ እንደዚሁም የሙከራ ቡድኑ 59.38 ነው፡፡ ይህ የውጤት ልዩነት በt-ቴስት ስታትስቲክስ (p= 0.046) ጉልህ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ እንደዚሁም ትኩረት በተደረገባቸው ንዑሳን የመጻፍ ክሂሎች ላይ የሙከራ ቡድኑ የቅድመና የድህረትምህርት አማካይ የፈተና ውጤቶች ልዩነት በt-ቴስት ስታትስቲክስ ተሰልቶ ውጤቱም በተሰጡ ቃላትና ሀረጋት ዐረፍተነገር በማዋቀር ንዑስ ክሂል (p= 0.001)፣ የዐረፍተነገር ክፍሎችን ቅደም ተከተል በማስተካከል ንዑስ ክሂል (p= 0.00)፣ ጅምር ዐረፍተነገሮችን በማጠናቀቅ ንዑስ ክሂል (p= 0.000)፣ አያያዥ ቃላትን ተጠቅሞ ዐረፍተነገርን በማደራጀት ንዑስ ክሂል (p= 0.000)፣ ጅምር አንቀጽን በማጠናቀቅ ንዑስ ክሂል (p= 0.00) ጉልህ ሆኗል፡፡ በሌላ በኩል ትብብራዊ መማር የተማሪዎችን ማህበራዊ ክሂልና የመጻፍ ተነሳሽነትን ለማሳደግ ያለው ተፅዕኖ ምን እንደሚመስል በጽሑፍ መጠይቅና በቃለመጠይቅ አማካይነት መረጃ ተሰብስቧል፡፡ ማህበራዊ ክሂልን በተመለከተ የጽሑፍ መጠይቁን ከሞሉ መላሾች መካከል 81.18% የሚሆኑት ማህበራዊ ክሂላቸው እንዳደገ በምላሻቸው ጠቁመዋል፡፡ ይህም ውጤት በt- ቴስት ተሰልቶ 4.31 አማካይ ውጤት አሳይቷል፡፡ ይህ ውጤት ደግሞ Peta (2001) ባስቀመጠው ቀመር መሰረት ከፍተኛ ነው፡፡ ከቃለመጠይቁም የተገኘው ምላሽ የጽሑፍ መጠይቁን ውጤት የሚያጠናክር ሆኗል፡፡ እንደዚሁም የመጻፍ ተነሳሽነትን በተመለከተ የጽሑፍ መጠይቁን ከሞሉ መላሾች መካከል 83.83% የሚሆኑት የመጻፍ ተነሳሽነታቸው እንዳደገ በምላሻቸው ጠቁመዋል፡፡ ይህም ውጤት በt- ቴስት ተሰልቶ 4.4 አማካይ ውጤት አሳይቷል፡፡ አሁንም ይህ ውጤት Peta (2001) ባስቀመጠው ቀመር መሰረት ከፍተኛ ነው፡፡ ከቃለመጠይቁም የተገኘው ምላሽ የጽሑፍ መጠይቁን ውጤት የሚያጠናክር ሆኗል፡፡ በአጠቃላይ ከጽሑፍ መጠይቁና ከቃለመጠይቁ ከተገኘው መረጃ መገንዘብ የተቻለው ትብብራዊ መማር የተማሪዎችን ማህበራዊ ክሂልንና የመጻፍ ተነሳሽነትን ለማሳደግ ያለው ተፅዕኖ ጉልህ መሆኑን ነው፡፡ በመሆኑም ትብብራዊ መማር የተማሪዎችን የመፃፍ ክሂልን፣ ማህበራዊ ክሂልንና የመፃፍ ተነሳሽነትን ለማሳደግ ያለው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ፣ የሚመለከታቸው አካላት ለማስተማሪያ ዘዴው ትኩረት ሊሰጡት እንደሚገባ አጥኚው ይጠቁማል፡፡Item ሂደተ ዘውጋዊ ዘዴ በተማሪዎች ድርሰት የመፃፍ ችልታ እና አመለካከት ላይ የሚኖረው ተፅህኖ፣ በምዕራብ ሸዋ አካባቢ በኤጀሬ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ9ኛ ክፍል ተተኳሪነት(አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ, 2009) ተካልኝ ለማ; ዶ/ር ሴይመ ከበደItem የቤተሰብ ዳራ የአንብቦ መረዳት ችሎታን የመተንበይ ድርሻ፤ በአምስተኛና በሰባተኛ ክፍል ተማሪዎች ተተኳሪነት(አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ, 2010) አስቴር አስራት ዳኘው; ዶ/ር ታመነ ኪቲላ; ዶ/ር ሙላት አስናቀየዚህ ጥናት ዋና አላማ የቤተሰብ ዳራ የአንብቦ መረዳት ችሎታን የመተንበይ ድርሻውን መለየት ነው፡፡ ተሳታፊዎች በዶና በርበር የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2010 ዓ.ም ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ የሚገኙ በዕጣ ንሞና የተመረጡ 151 የአምስተኛና 170 የሰባተኛ ከፍል ተማሪዎች ናቸው፡፡ ከተሳታፊዎች መረጃ የተሰበሰበው በሶስት የተለያዩ የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴዎች ነው፡፡ እነሱም የጽሁፍ መጠይቅ፣ ፈተናና የቡድን ውይይት ናቸው፡፡ ፈተናው አንብቦ መረዳት ችሎታን፣ መጠይቁ የቤተሰብ ዳራን ለመለካት ሲያገለግል የቡድን ውይይቱ ደግሞ ተጨማሪ የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴ በመሆን አገልግሏል፡፡ የተሰበሰቡት መረጃዎች አስተማማኝነት፣ ተገቢነትና የውጤት ስርጭት ወጥነት ተሰልቶ ከተረጋገጠ በኋላ ሁሉም መረጃዎች በተንባይና ገላጭ ስታትስቲክሶች አማካኝነት ተተንትነው ተብራርተዋል፡፡ የተገኘው መረጃ የፓራሜትሪያዊ መፈተሻ ዘዴዎችን ለመጠቀም የሚያስችል በመሆኑ ተግባራዊ የተደረጉት የመተንተኛ ዘዴዎች የህብረ ድህረት ትንተናና የነጻ ናሙና ቲቴስት ናቸው፡፡ በትንተናው መሰረት የቤተሰብ ዳራ የአንብቦ መረዳት ችሎታን ጉልህ ተንባይ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ከቤተሰብ ዳራ ዝርዝር ተላውጦዎች የአንብቦ መረዳት ችሎታን በከፍተኛ ደረጃ የተነበዩት የቤተሰብ የኢኮኖሚ ደረጃና የቤተሰብ የትምህርት ደረጃ ናቸው፡፡ የቤተሰብ የኢኮኖሚ ደረጃ መለኪያ የሆኑት ወርሀዊ ገቢና ß= 0.5ና ገቢ ከአካባቢ ጋር ሲነጻጸር ß= 0.119 የቤተሰብ የትምህርት ደረጃ ß= 0.382 ከፍተኛ የመደበኛ ቤታ ዋጋ በማምጣት ከሌሎች ተላውዎች በተሻለ ጉልህ ተንባይ ሆነዋል፡፡ ይህ ውጤት በሁለቱም የክፍል ደረጃ ተቀራራቢ ሆኖ ተገኝቷል፡፡ በተጨማሪነት የታየው ሌላው ጥያቄ የአንብቦ መረዳት ችሎታ በጾታ ልዩነት እንዳለው መቃኘት ሲሆን የወንዶች አማካኝ ችሎታ ከሴቶች የተሻለ ሆኖ ቢገኝም በሁለቱ መካከል ያለው ልዩነት ጉልህ እንዳልሆነ በትንተናው ተረጋግጧል፡፡ የአምስተኛ ክፍል ተማሪዎች ወንዶች 22.51 ሲሆን የሴቶቹ 21. 63 የሰባተኛ ክፍል ወንዶች 17.74 የሴቶች 17.13 ሆኖ ተገኝቷል፡፡ ከዚህ ውጤት በመነሳትም በትምህርት ቤት ውስጥ የኢኮኖሚ ችግር ያለባቸውን ልጆች ድጋፍ ማድረግና ያልተማሩ ወላጆችን የተለያዩ የመሰረታዊ ትምህርት እንዲያገኙ ማድረግ የሚሉ የመፍትሄ ሀሳቦች ተሰጥተዋል፡፡ ለሴቶች የተለያዩ ድጋፎችን መስጠት የሚል ስነትምህርታዊ አንድምታ ተሰጥቷል፡፡ በተጨማሪም በረጅም ጊዜ የጥናት ስልት፣ ወላጆችንና መምህራንን ተሳታፊ በማድረግ፣ አጠቃላይ ከአንድ እስከ ስምንት የሚገኙ ተማሪዎችን በማካተት እንዲም በርካታ ናሙና ወስደው ማጥናት ይቻላል የሚሉ የምርምር ጥቆማዎችም ተሰጥተዋል፡፡Item መስተጋብራዊ የማስተማሪያ ዘዴ መስማት በተሳናቸው ተማሪዎች የመጻፍ ክሂሌ ችሎታና የመማር ፍላጎት ላይ ያለው ተጽዕኖ (በሰባተኛ ክፍል ላይ የተካሄደ ሙከራዊ ጥናት)(አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ, 2016) እታገኝ ገደፋው ጌታሁን; ዶ/ር ጌታቸው እንዳላማውየዚህ ጥናት ዋነኛ ዓላማ መስተጋብራዊ የማስተማሪያ ዘዴ መስማት የተሳናቸው ተማሪዎችን የመጻፍ ክሂሌ ችልታና የመማር ፍላጎት ከማሻሻል አንጻር ያለውን ተጽዕኖ መመርመር ነው፡፡ ጥናቱ በአንዴ የሙከራ ቡድን ንድፍ (Single Group Experimental Design) ላይ በመመስረት የተከናወነ ሲሆን ይህ የምርምር ንድፍም የጥናት ናሙናን በመምረጥ ሂደት የተጠኚዎች ቁጥር ለሁለት ቡድን ማለትም ለጥብቅ (Control) ለሙከራ (Exprmental) ሳይበቃ ሲቀር የሚመረጥ ነው፡፡ ጥናቱ የተካሄደው በአዱስ አበባ መስተዲድር ስር ከሚገኙ መስማት የተሳናቸው ተማሪዎች ትምህርት ቤቶች መካከል በአሌፋ መስማት የተሳናቸው ተማሪዎች የመጀመሪያ ደረጃ ልዩ ትምህርት ቤት ሲሆን በትምህርት ቤቱ ከሚገኙ የክፍል ደረጃዎች መካከል ለጥናቱ የተመረጠው ክፍል ሰባተኛ ነው፡፡ ትምህርት ቤቱንና የክፍል ደረጃውን በመምረጥ ረገድ አላማ ተኮር ናሙና (purposive Sampling) ተግባራዊ ተደርጓሌ፡፡ በጥናቱ ተሳታፊ የሆኑት ተማሪዎች በጠቅላይ ናሙና (Comprehensive Sampling) የተመረጡ ሲሆን በዘህም በክፍል ደረጃው የሚማሩ ሁሉም ተማሪዎች (ሰባቱም) በጥናቱ ተካተዋል፡፡ እነዘህ ተማሪዎች በቀጥታ በጥናቱ እንዲሳተፉ የተደረገበት ዋናው ምክንያት ቁጥራቸው ውስንና ከተጠቀሰው በላይ ባለመሆኑ ነው፡፡ለጥናቱ በመረጃ መስብሰቢያ ዘዴነት ተግባር ላይ የዋሉት ፈተና፣ የጽሑፍ መጠይቅና የተማሪዎች የቡድን ተኮር ውይይት ናቸው፡፡ ፈተናው ቅድመና ድህረ ትምህርት ፈተና ሲሆን ዋነኛ አላማውም ተጠኚ ተማሪዎች በመስተጋብራዊ የማስተማሪያ ዘዴ ከመማራቸው በፈትና በኋላ የነበራቸው የመጻፍ ክሂል ትምህርት የመማር ፍላጎት ምን ያህል ጉልህ ልዩነት እንዳሳየ ማረጋገጥ ነው፡፡ ሌላኛው የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴ ሆኖ ያገለገለው የቡዴን ተኮር ውይይት ሲሆን አላማው ደግሞ በፈተናና በጽሁፍ መጠይቅ ለተሰበሰቡት መረጃዎች ማጠናከሪያ ሀሳብ ማስገኘት ነው፡፡ በዚህም መሰረት የመጻፍ ክሂል ፈተናውና የጽሁፍ መጠይቁ በቅድመና ድህረ ትምህርት ትግበራው ላይ ለተጠኚዎች ቀርበው መረጃ የተሰበሰበባቸው ሲሆን የተገኘው ውጤትም በጥንድ ናሙና ቲ- ቴስት (Paird sample t-test) መጠናዊ የመረጃ መተንተኛ ስሌት ተሰሌቶ ( P< 0.05) የሆነ የጉልህነት መለያ ውጤት ተገኝቷል፡፡ በአንጻሩ በቡድን ተኮር ውይይቱ የተሰበሰበው መረጃም በአይነታዊ የመረጃ መተንተኛ ዘዴ ተተንትኖ በፈተናውና በጽሁፍ መጠይቁ የተገኘውን የሚደግፍ ውጤት አስገኝቷል ፡፡ በአጠቃላይ በሶስቱ የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴዎች ተሰብስበው ከተተነተኑት መረጃዎች የተገኘው ውጤት የሚያመለክተው መስተጋብራዊ የማስተማሪያ ዘዴ መስማት በተሳናቸው ተማሪዎች የመጻፍ ክሂል ችሎታና የመማር ፍላጎት ላይ የሚያሳድረው ተጽእኖ መኖሩንና ተጽዕኖውም አዎንታዊ መሆኑን ነው፡፡Item በቴክስት ውቅር ብልሃቶች በዐማርኛ ማንበብን መማር በተማሪዎች የአንብቦ መረዳት ችሎታ ላይ ያለው ተጽዕኖ- በስድስተኛ ክፍል ተተኳሪነት(አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ, 2009) እንድሪስ ዓባይ ደሊሉ; ዶ/ር ማረው ዓለሙየጥናቱ ዋና ዓላማ በቴክስት ውቅር ብልሃቶች ማንበብን መማር በተማሪዎች የማንበብ ተነሳሽነት፣ የማንበብ ግለብቃት እምነት፣ የማንበብ ትኩረትና የአንብቦ መረዳት ችሎታ ላይ ያለውን ቀጥተኛና ኢቀጥተኛ ተጽዕኖ መፈተሽ ነው፡፡ ዓላማውን ለማሳካትም መጠናዊ ምርምር ብሎም ፍትነትመሰል የጥናት ንድፍ ተግባራዊ ሆኗል፡፡ በመሆኑም በቴክስት ውቅር ብልሃቶች፣በብልሃትአልባ የቴክስት ውቅር እውቀትና አዘውትሮ በስራ ላይ በሚውለው የማንበብ ትምህርት አቀራረቦች ሦስት ቡድኖች ተለያይተው የአንብቦ መረዳት ትምህርትን በ12 ሳምንታት ለ24 ክፍለጊዜያት እንዲማሩ ተደርጓል፡፡ የጥናቱ ተሳታፊዎችም በደሴ ከተማ በአዲስፋና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርትቤት በ2009 ዓ.ም በመማር ላይ ከሚገኙ አራት የስድስተኛ ክፍል መማሪያ ክፍሎች ውስጥ በተራ እጣ ንሞና ዘዴ የተመረጡ ሦስት መማሪያ ክፍሎች ማለትም በብልሃት ቡድኑ 44፣ በብልሃትአልባ ቡድኑ 45፣ በቁጥጥር ቡድኑ 46 በጥቅሉ 135 ተማሪዎች ናቸው፡፡ ከተሳታፊዎቹም ቅድመትምህርትና ድህረትምህርት የአንብቦ መረዳት ውጤት፣ የማንበብ ትኩረት፣ የማንበብ ተነሳሽነትና የማንበብ ግለብቃት እምነት በፈተናዎችና በመጠይቆች አማካይነት መረጃዎች ተሰብስበዋል፡፡ መረጃዎቹም በአማካይ ውጤት፣ በመደበኛ ልይይት፣በአበርልይይት ብሎም የድኅረት ስሌት መሰረት ባለው የHayes (2013) ፕሮሰስ ፕላግኢን ኤስ.ፒኤስ.ኤስ (Hayes PROCESS plugin SPSS) ባለትይዩ የደንጋጊ ተላውጦዎች ትንተና ሞዴል 4 ተሰልተው ተተንትነዋል፡፡ የጥናቱ ግኝቶች እንዳመላከቱትም በሌሎቹ ሁለት አቀራረቦች ከተማሩት ተማሪዎች ይልቅ በቴክስት ውቅር ብልሃቶች ማንበብን የተማሩት በአንብቦ መረዳት ውጤታቸው፣ በማንበብ ተነሳሽነታቸው፣ በማንበብ ግለብቃት እምነታቸውና በማንበብ ትኩረታቸው ጉልህ መሻሻል አሳይተዋል፡፡ እንዲሁም የቴክስት ውቅር ብልሃቶች ትምህርት በአንብቦ መረዳት ውጤት ላይ ለሚያሳድረው ተጽዕኖ የማንበብ ትኩረትና የማንበብ ተነሳሽነት ከፊል የደንጋጊነት ሚና ሲያሳዩ የማንበብ ግለብቃት እምነት ግን ደንጋጊነቱ ጉልህ ሆኖ አልተገኘም፡፡ ከጥናቱ ግኝቶች በመነሳትም በቴክስት ውቅር ብልሃቶች ማንበብን መማር የተማሪዎችን የአንብቦ መረዳት ውጤት፣ የማንበብ ተነሳሽነት፣ የማንበብ ግለብቃት እምነትና የማንበብ ትኩረት ያሻሽላል ወደሚል ድምዳሜ ተደርሷል፡፡ ከዚህም ሌላ የቴክስት ውቅር ብልሃቶች ትምህርት በተማሪዎች የማንበብ ትኩረትና የማንበብ ተነሳሽነት ላይ የሚያስከትለው መሻሻል ኢቀጥተኛ በሆነ መንገድም የአንብቦ መረዳት ውጤት ከፍ እንዲል ያደርጋል ወደሚል መደምደሚያ ተደርሷል፡፡ ከጥናቱ ግኝቶች በመነሳትም ስነትምህርታዊ የመፍትሄ ሀሳቦች ተጠቁመዋል፤ የወደፊት የምርምር አቅጣጫዎችም ተመላክተዋል፡፡Item የመማሪያ ክፍል የድርድር ዲስኩር መንስኤ፣ ብልሃትና መፍትሔ ትንተና(አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ, 2009) ከበደ ይመር ይማም; ዶ/ር ዓማኑኤል ገብሩየዚህ ጥናት ዋና ዓላማ በአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ክፍለጊዜያት የሚካሄደውን የድርድር ዲስኩር መንስኤ፣ ብሌሃትና መፌትሔ በመተንተን የመስተጋብሩን ሂደት መረዳት ነው፡፡ የጥናቱ መነሻ ጥያቄዎችም ለድርድር ክንውን መነሻ የሚሆኑት መንስኤዎች ምን ምን ናቸው? ለድርድር ክንውኑ መነሻ የሆኑት ችግሮች መፌትሔ የሚያገኙባቸው ብልሃቶችስ ምን ምን ናቸው? የዴርዴር ክንውኑ እንዲሳካ እና እንዳይሳካ የሚያደርጉት ተለዋዋጮች ምን ምን ናቸው? የሚሉት ናቸው፡፡ እነዙህን ጥያቄዎች በአግባቡ መመለስ እንዲቻልም ዓይነታዊ የምርምር ዘዴን በመከተል የንግግር ልውውጥ ትንተና አቀራረብ ተግባራዊ ተደርጓሌ፡፡ በዚህ አቀራረብ መሠረት፣ በደብረብርሃን ከተማ በሚገኙ ሦስት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እና ሰባት የዘጠነኛ ክፍል የአማርኝ ቋንቋ መምህራን በዓላማ ተኮር የንሞና ስሌት ተመርጠዋል፡፡ እነዚህ መምህራን በክፍል ውስጥ ገብተው ሲያስተምሩ ለሃያ አንድ ክፍለጊዛያት በመቅረጸምሥል ከተሰበሰበው መረጃ መካከል አስራ አራቱ ወደምዝግብ መረጃነት ተቀይረዋል፡፡ በድርድር ክንውን ሞዴል መሠረት ለትንተናው የሚሆኑ ውሁዳሃዶችም ከምዝግብ መረጃው ተለይተውና የጥናቱን ጥያቄዎች መመለስ በሚያስችለበት መንገድ በሦስት ከተከፈሉ በኋላ በመናገር ተራ ልውውጥ ሥርዓት ተተንትነዋል፡፡ የጥናቱ ውጤቶችም፣ በድርድር ክንውኑ መነሻ የሆኑት መንስኤዎች ሰዋስው ነክ ጉዳዮች፣ ተገቢ ያልሆኑ የቃላት ምርጫ፣ ቋንቋ ነክ ፅንሰሐሳቦች፣ የተባለውን በትክክል አለማዳመጥ፣ የግሌጽነት መጓደል፣ መላምትን ማረጋገጥ እና ተጨማሪ መረጃ መሻት ናቸው፡፡ ስለዚህ የድርድር ክንውን የተማሪዎቹን የቋንቋ ግብኣት፣ የቋንቋ አፍልቆትና የግብረመልስ ፍላጎት ለማሟሊት ሲባል ተከናውኗል፡፡ ችግሮቹ ተስተካክለው መፍትሔ ያገኙባቸው ብሌሃቶችም አእምሯዊና ማህበራዊ ባህሪ ያላቸው ናቸው፡፡ አእምሯዊ ብልሃቶች ማስተጋባት፣ ማውጣጣት፣ ማስሞላትና ማብራሪያ መጠየቅ ሲሆኑ ማኅበራዊ ብሌሃቶቹ ደግሞ ማመሳከር፣ እገዛ መሻት፣ አብሮ ማዋቀር፣ መደጋገፍ፣ መፍካከር፣ ሣቅና ዝምታ ናቸው፡፡ ስለዚህ ተሳታፊዎቹ ያጋጠሟቸውን ችግሮች በድርድር ክንውን ለመፍታት እንዳስፈላጊነታቸው አእምሯዊና ማኅበራዊ ብልሃቶችን እያሰባጠሩ ተገልግለውባቸዋል፡፡ የድርድር ክንውኑ እንዲሳካ እና እንዳይሳካ ያደረጉት ተለዋዋጮችም ተገኝተዋል፡፡ የተሳካ ያደረጉት ለመረዳት እንከኖች ትኩረት መስጠት፣ ድጋፍ ማዴረግ፣ ትምህርታዊ ባህሪን መሊበስ፣ የንግግር ልውውጡን በአግባቡ መምራት፣ በፍሊጎት መሳተፍና በቂ የመናገሪያ ጊዜ መስጠት ናቸው፡፡ ስለዚህ እነዙህ ብልሃቶች ለትምህርቱ ስኬታማነት አስተዋጽኦ ያደረጉ ጠንካራ ጎኖች ናቸው፡፡ በአንጻሩ ግልጽ እርማት፣ አስተካክሎ መድገም፣ መልመጃው ከተማሪዎቹ ችሎታ በላይ ወይም በታች መሆን፣ በተሳታፊዎቹ መካከል የችሎታ ልዩነት አለመኖር፣ የቆይታ ጊዜና የእገዛ ማነስ እንዲይሳካ ያደረጉት ተለዋዋጮች ናቸው፡፡ ስለሆነም እነዚህ ብሌሃቶች በመስተጋብሩ ላይ ችግር መኖሩን ጠቁመዋል፡፡ የጥናቱን ውጤት መሠረት በማድረግም የመምህራን ትምህርት ሥልጠና ሲዘጋጅ በድርድር ክንውን ሳቢያ ለሚገኘው ትምህርታዊ ፊይዲ ትኩረት ቢሰጥ፣ መልመጃዎች የተማሪውን የአእምሮ ቀሪብ ዕድገት የሚመጥኑ ሆነው ቢዘጋጁ፣ የአማርኛ ቋንቋ መምህራን የክፍል ውስጥ መስተጋብራቸውን በመቅረጸምሥሌ በመቅረጽ፣ በመተንተንና በማንጸባረቅ የማስተማር ዘዴያቸውን ይበልጥ ያሻሽሉ ዘንድ ሥልጠና ቢሰጣቸው የሚሉ አስተያየቶች ቀርበዋል፡፡ በመጨረሻም የዴርዴር ክንውን በተለያዩ ዓውድች ጥናት ይደረግበት ዘንድ የሚያመለክቱ የምርምር ጉዲዮች ተጠቁመዋል፡፡Item በአማርኛ ቋንቋ ትምህርት የተማሪዎች የራስመር መማር ብልሃቶች አጠቃቀም፣ የማንበብ ግለብቃት እምነት እና አንብቦ የመረዳት ችሎታ ጾታ ተኮር ተዛምዶ፤ በተመረጡ የአስራአንደኛ ክፍል አፍፈት ተማሪዎች ተተኳሪነት(አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ, 2016) ይድነቃቸው ገረመው ዓለሙ; (ዶ/ር) ገረመው ለሙ; (ዶ/ር) ሰይድ ይመርበአማርኛ ቋንቋ ትምህርት የተማሪዎች የራስመር መማር ብልሃቶች አጠቃቀም፣ የማንበብ ግለብቃት እምነት እና አንብቦ የመረዳት ችሎታ ጾታ ተኮር ተዛምዶItem የአርቲስት ፀጋዪ ስሜ ባህላዊ ዘፈኖች ይዘት ትንተና(አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2002-06) ሜሮን ውንዳ; ገዛኸኝ ጌታቸውItem የገፀ-ባህርያት አሳሳል በከርታታው ልቦለድ(አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ, 2001-06) ሳሙኤል ደመቀ; ሰላማዊት መካይህ ጥናት “የገፀ-ባህርያት አሳሳል በከርታታው ልቦለድ” በሚል ርዕስ፣ በ1999 ዓ.ም በደራሲ ባህሩ ዘርጋው የታተመውን ከርታታው በጥናቱ ውስጥ የደራሲው የገፀ-ባህርያት አሳሳል እንዴት እንደሆነ ከመታየቱ በፊት ከዚህ ጥናት አስቀድሞ በገፀ-ባህርያት አሳሳል ላይ የተሰሩ የተዛማጅ ፅሁፎች ቅኝት ተደርጓል፡፡ ከዚያም ስለገፀ-ባህርያት አሳሳል ስልት ትወራዊ ዳራ ተሰጥቷል፡፡ ረጅም ልቦለድ ይመለከታል፡፡የጥናቱ መነሻ ደራሲው ለመጀመሪያ ጊዜ ባሳተሙት በዚህ ልቦለድ ውስጥ ያሉ ገፀ-ባህርያትን እንዴት እንደሳሉ ለመተንተን እና በገፀ-ባህርያት አሳሳል ወቅት ያሳዩት ድክመትም ሆነ ጥንካሬን ለመገምገም ነው፡፡ ከዚያም በተጨማሪ ደራሲው አዲስ የገፀ-ባህርያት አሳሳል ስልት መጠቀማቸውን ለማሳየት ነው፡፡በድርሰቱ ውስጥ ገፀባ-ህርያቱን ለመሳል በአንደኛ መደብ የትረካ አንጻር (እኔ ባይ) ተራኪ በስፋት ይታያል፡፡በዚህ ልቦለድ ውስጥ ደራሲው ትኩረት የሰጡበትና ጠንከር ብሎ የታየው ጉዳይ የገፀ-ባህርያት ውስጣዊ ባህሪ ላይ ሲሆን በአካላዊ ገለፃው ረገድ ደከም ብሎ ይታያል፡፡ ከንዑስ ገፀባ-ህርያት ይልቅ በዋና ገፀባ-ህርያት ላይ የተጠቀሙት አካላዊ ገለፃ ይህ ነው የሚባል አይደልም፡፡በልቦለዱ የታየው የገፀባ-ህርያት አሳሳል ስልት እንብዛም ሆኖ ተገኝቷል፡፡ አብዛኛዎቹ ገፀባ-ህርያት ውጫዊ መልካቸውና ውስጣዊ ባህሪያቸው ተመሳሳይ መሆኑ ገፀ-ባህርያቱን ወደ ግጭት እንዳይገቡ ስላደረጋቸው የገሀዱ አለም ነፀብራቅ ይሆኑ ይሆን? የሚል ጥያቄ ያስነሳል፡፡ አንዳንዶቹ ገፀባ-ህርያት ወጥነት የጐደላቸውና ኢተአማኒ ናቸው፡፡ በመጽሐፉ የታየው ሙት መንፈስን የወከለው ገፀ-ባህሪ ለአገራችን አንባቢያን አዲስ በመሆኑ ስለሙት መንፈስ በመጠኑም እንዲያውቅ በመደረጉ ይደነቃል፡፡በመጨረሻም ይህ ጥናት በጥናቱ ማጠቃለያ ስር የዚህን ልቦለድ ድክመትና ጥንካሬ በማውጣት ለማሳየት ሞክሯል፡፡ ገፀ-ባህርያቱ በአብዛኛው ተመሳሳይ አካላዊ መልክና ሕኒናዊ ባህሪ መያዛቸው ልቦለዱን ከድርሰት አፃፃፍ አንፃር ደካማ ሲያደርገው፤ በመጽሐፉ የተሳሉት ብዙዎቹ ገፀ-ባህርያት ቆራጥነታቸውና የአላማ ጽናታቸው እስከ ታሪኩ መጨረሻ መዝለቁ ከዘላቂነት አንፃር መጽሐፉ ያሳየው ጥንካሬ ነው፡፡Item “የጦር ሜዳ ውሎ” በተሰኘው የብርጋዴል ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም መጽሐፍ ላይ ከግለ-ታሪክ አጻጻፍ አንጻር የተደረገ ትንተና(አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ, 2001-06) እታፈራሁ በየነ; ብርሃኑ ገ/ማርያም