የሴቶች ተሞክሮ በተመረጡ የአማርኛ ግለታሪኮች

No Thumbnail Available

Date

2024-08

Journal Title

Journal ISSN

Volume Title

Publisher

አዲስ አበባ ዩኒቨርሰቲ

Abstract

የዚህ ጥናት ዋና ዓላማ በተመረጡ የሴቶች ተሞክሮ በአማርኛ ግለ ታሪክ ፍተሻ ነው፡፡ ጥናቱ ንድፍ አይነታዊ ገላጭ የጥናት ንድፍ የተከተለ ነው፡፡ የመረጃ ምንጮች ሁለተኛ ደረጃ (ዳህራይ) የመረጃ ምንጭ ነው፡፡ ይህም ማለት በግለሰቦች በግላቸው የተፃፉ የአማረኛ ግለ ታሪኮች ትሙት ግድ የለም በዶ/ር ትግስት ግርማ ፣የፀሐይ ጉዞ ወ/ሮ ፀሐይ ይትባረክ የውብ የውብ ድንበር እውተኛ ታሪክ በወ/ሮ ውብ ድንበር ነጋሽ የተፃፈ የአማረኛ ግለ ታሪክ መጽሀፍት መሰረት አድርጎ የተሰራ ጥናት ነው፡፡ የናሙና አመራረጥ አላማ ተኮር ነው፡፡ የተመረጡ የአማረኛ ግለ ታሪክ መፅሀፍት በዓላማ በራሱ አነሳሽነት በቀላሉ በገበያ ላይ የሚገኙ የቅርብ የታተሙ መጽሀፍት በመሆኑ ጭምር ነው፡፡ የመረጃው ትንተና ዘዴ ይዘት ትንተና ላይ አተኩሯል፡፡ ማለትም በመጽሀፍ ውስጥ የተካተቱ በተለዩት ርእሰ ጉዳዮች አንፃር ተተንትኗል፡፡ በዚህ ባሻገር ግለ ታሪኮች በእንስታዊ (ሴትነት ግዴ ትግል) አንፃር በአምስት ቁልፍ ርእሰ ጉዳዮች ማለትም ፓትሪያሊክ(አባዊ) ሥርአት ኢንተርሴክሽናሊቲ ፣የሥርአት ፆታ አፈጻፀም፣ ማህበራዊ ግንባታና የወንድ ዕይታ በሚሉ ርእሰ ጉዳዮች አንፃር ፍተሸ ተደርጋል፡፡ በመሆኑም ግለ ታሪክ አፃፃፍ ላይ የሚመለከተው ክፍል ትኩረት ቢያደርግ የሕይወት ተሞክሮ ማህራዊ ግንኙነት እና የፆታ እኩልነት እዲሁም ጥበብና ትምህርትን በማስፋት ከጾታ ጋር ተያያዞ የሚፈጠሩ ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ፣ፖለቲካዊ ችግሮች ላይ መፍትሔ ለማበጀት ይረዳል፡፡ ቁልፍ ቃላት ፡- የሴቶች ተሞክሮ፣ ግለ ታሪክ አማርኛ እንስታዊ ጽንሰ ሀሳብ፡፡

Description

Keywords

Citation