ፕሮጀክት ተኮር መማር፣ በመጻፍ ችሎታና ተነሳሽነት ላይ ያለው ተፅዕኖ፤ በ10ኛ ክፍል አማርኛ ቋንቋ አፍፈት ተማሪዎች ተተኳሪነት
No Thumbnail Available
Date
2016
Authors
Journal Title
Journal ISSN
Volume Title
Publisher
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
Abstract
የዚህ ጥናት ዓላማ ፕሮጀክት ተኮር መማር፣ ለተማሪዎች የመጻፍ ችሎታእናተነሳሽነትመሻሻል ያለውን ሚና መፈተሽ ነው፡፡ ዓላማውን ከግብ ለማድረስምቅድመትምህርትናድኅረ ትምህርት ፈተና ባለቁጥጥር ቡድን ከፊል ሙከራዊ (quasi-expermental) ስልትተግባራዊ ሆኗል፡፡ በጥናቱ የትግበራ ሂደትም አማራ ክልል በአላማተኮርንሞናተመርጧል፤ ደብረማርቆስ ከተማ የሚገኘው ንጉስ ተክለሃይማኖትአጠቃላይሁለተኛደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ደግሞ በአመቺ ንሞና ከተመረጠበኋላ በዚህትምህርትቤት የሚገኙ የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች በዕጣ ተመርጠው ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ ክልሉበዓላማተኮር ንሞና የተመረጠው ጥናቱ አፍፈት ተማሪዎች ላይ የሚያተኩርበመሆኑነው።ትምህርት ቤቱ በአመቺ ንሞና የተመረጠበት ምክንያትምጥናቱከፊልፍትነታዊእንደመሆኑ መጠን ትምህርት ቤቱን እና የአማርኛ ቋንቋ መምህራንን ልዩትብብርእናድጋፍ የሚፈልጉ ጉዳዮችን የሚጠይቅ በመሆኑ ለዚህም የትምህርትቤቱአስተዳደር፣መምህራንና ተማሪዎች ለጥናቱ ፈቃደኛ በመሆናቸው ነው፡፡ የ10ኛ ክፍልተማሪዎችበዕጣየተመረጡበት ምክንያት ደግሞ ከ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በስተቀር ጥናቱበ9ኛ፣ 10ኛእና11ኛ ክፍል ተማሪዎች ላይ ቢካሄድ በተማሪዎች መረጃ የመሰብሰብሂደትላይችግርአይኖርም ተብሎ ስለታሰበ ነው፡፡ መረጃዎች ከተሳታፊ ተማሪዎችበመጻፍችሎታፈተናእና በመጻፍ ተነሳሽነት የጽሑፍ መጠይቅ ተሰብስበዋል፡፡ የተገኙትመረጃዎችምየመተንተኛ ስልቱ እሙኖች በገላጭ ስታቲስቲክስ ከተፈተሹ በኋላ በሙከራናበቁጥጥርቡድኖች መካከል ልዩነት መኖር አለመኖሩን ለመፈተሽ የቅድመና ድኅረትምህርትአጠቃላይ የመጻፍ ችሎታ፣ ንዑሳን ችሎታዎች (ይዘት፣ አደረጃጀት፣ የቃላትአመራረጥናአጠቃቀም፣ የቋንቋ አጠቃቀም እና ስርዓተ አጻጻፍ) አማካይ ውጤቶችና የመጻፍተነሳሽነትየጽሑፍ መጠይቅ አማካይ ውጤቶች በባለብዙ ተላውጦ ልይይትትንተናዘዴ(Multivariate Analysis of Variance, MANOVA) ተሰልተውተተንትነዋል፡፡ በተገኙትውጤቶች መሠረትም፣ የተማሪዎች አጠቃላይ የመጻፍ ችሎታእና ንዑሳንችሎታዎች(ይዘት፣ አደረጃጀት፣ የቃላት አመራረጥና አጠቃቀም፣ የቋንቋ አጠቃቀምእናስርዓተአጻጻፍ) እንዲሁም የመጻፍ ተነሳሽነት የጽሑፍ መጠይቅ ውጤቶችየሙከራቡድንተማሪዎች ከቁጥጥር ቡድን ተማሪዎች አማካይ ውጤቶች ተሽለውና ጉልህ (p<.05) ልዩነትያላቸው ሆነው ተገኝተዋል። በዚህም መሠረት ፕሮጀክት ተኮር መማርየተማሪዎችንአጠቃላይ የመጻፍ ችሎታ እና ንዑሳን ችሎታዎች እንዲሁም የመጻፍተነሳሽነትለማሻሻልሚና እንዳለውና ሚናውም ከፍተኛ እንደሆነ ጥናቱ አሳይቷል፡፡ በመሆኑም፣ የመጻፍትምህርትን በፕሮጀክት ተኮር መማር ተግባራት ማቅረብ እንደሚያስፈልግተጠቁሟል፡፡
Description
Keywords
ፕሮጀክት ተኮር መማር፣ በመጻፍ ችሎታና ተነሳሽነት ላይ ያለው ተፅዕኖ