የድጋፍ ብልሃቶች በአንብቦ የመረዳት ችሎታ እና ግለመር ማንበብ ላይ ተፅዕኖ፤ በ7ኛ ክፍል ተማሪዎች ተተኳሪነት

dc.contributor.advisorፕሮፌሰር ተስፋየ ሸዋየ
dc.contributor.authorራሔል ሲሳይ ተገኘ
dc.date.accessioned2025-07-23T07:35:38Z
dc.date.available2025-07-23T07:35:38Z
dc.date.issued2016
dc.description.abstractየዚህ ጥናት ዓላማ የድጋፍ ብልሃቶች የተማሪዎችን በአማርኛ ቋንቋ አንብቦ የመረዳት ችሎታ እና ግለመር ማንበብ ላይ ያላቸውን ተፅዕኖ መፈተሸ ነበር፡፡ ጥናቱ በዓይነቱ ቅደምተከተላው ቅይጥ (በአመዛኙ መጠናዊ) ሲሆን ቅድመና ድህረ ትምህርት በለቁጥጥር ቡድን ፍትነት ቡድን ፍትነት መሰል ንድፍን የተከተለ ነው፡፡ በ2015 ዓ.ም በአዲስአበባ ከተማ አስተዳደር፡ በጉለሌ ክፍለ ከተማ በአድስተስፋ አንደኛ ደረጃ ትምህርትቤት የ7ኛ ክፍል ተማሪዎች ተሳትፈዋል፡፡ መረጃዎችን ለመሰብሰብም አንብቦ የመረዳት ችሎታ ፈተናና የግለመር ማንበብ መጠይቅ ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡ ሌላው በአግዥነት ድህረቡድን ተኮር ውይይት ተግባራዊ ሆኗል ፡፡ እንዲሁም ሁለቱ ቡድኖች በተቀመጠላቸው የማስተማሪያ መንገድ መማርቸውን ለማረጋገጥ ሲባል ምልከታ ተካሂዷል ፡፡በቅድመ ፈተናና መቅድመ የጽሑፍ መጠይቅ የተገኙ ውጤቶች በጥንድና ነፃ ቲ-ትስቶች የትንተና ስልት እንዲሁም በድኀረ ፈተናና በድኀረ የጽሑፍ መጠይቅ የተገኙ ውጤቶች በጥንድ፡ ነፃ ቲ- ትስቶችና በአበር ልይይት ትንተና ስልቶች ተተንትነዋል፡፡ በተጨማሪም ከድህረቡድን ተኮር ውይይት የተገኙት ውጤቶችም እንደሚያመለክቱት በቅድመፈተናና በቅድመየጽሑፍ መጠይቅ ቡድኖች ተመጣጣኝ አማካይ ውጤቶች ያስመዘገቡ ሲሆን በድኀረ የጽሑፍ መጠይቅ ገለመር ማንበብ የሙከራ ቡድኑ ተማሪዎች ከቁጥጥት ቡድኑ ተማሪዎች ጉልህ የሆነ ልዩነት አሳይተዋል (P= <0.05):: ይህም ውጤት በድጋፍ ብልሀቶች መማር የተማሪዎችን አንብቦ የመረዳት ችሎታና ግለመር ማንበብን ከማሻሻል አኳያ ጉልህ አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቁሟል፡፡ በተገኙት ውጤቶች በመመስረት የመፍትሄ ሀሳቦችና የጥናት ጥቆማዎች ተሰጥተዋል፡፡
dc.identifier.urihttps://etd.aau.edu.et/handle/123456789/5675
dc.language.isoam
dc.publisherአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
dc.subjectየድጋፍ ብልሃቶች በአንብቦ የመረዳት ችሎታ እና ግለመር ማንበብ ላይ ተፅዕኖ
dc.titleየድጋፍ ብልሃቶች በአንብቦ የመረዳት ችሎታ እና ግለመር ማንበብ ላይ ተፅዕኖ፤ በ7ኛ ክፍል ተማሪዎች ተተኳሪነት
dc.typeThesis

Files

Original bundle
Now showing 1 - 1 of 1
No Thumbnail Available
Name:
ራሔል ሲሳይ ተገኘ.pdf
Size:
2.55 MB
Format:
Adobe Portable Document Format
License bundle
Now showing 1 - 1 of 1
No Thumbnail Available
Name:
license.txt
Size:
1.71 KB
Format:
Item-specific license agreed to upon submission
Description: