የባሕረ ሐሳብ እወጃ ፎክሎርነት
No Thumbnail Available
Date
2000-06
Authors
Journal Title
Journal ISSN
Volume Title
Publisher
አዲስ አበባ ዮኒቨርሲቲ
Abstract
በኢትዮጽያ በዓመቱ የአዲስ ዓመት መባቻ ለመቀበል ከሚደረጉት ክብረ በዓላት አንዱ በሃይማኖታዊ ሥነ-ሥዓርት የሚከበረዉ ቅዱስ ዮሐንስ ርእስ ዐውደ ዓመት ነው፡፡
በኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አጥቢያዎች በቅኔ ማሕሌትና በዐዉደ ምሕረት በሚኖረው ሥነ ሥርዓ ት ከትንሣኤ ጋር የተያያዙ የየዘመኑ አጽዋማትና አዓላት የሚታወቁበት፤ የባሕረ ሐሳብ እወጃና ዘመኑ መለወጡ የሚበሰርበት መንገድ ፎክሎርነት ያለው መሆኑ ጥናቱ ያሳያል፡፡ ይህ ‹‹የባሕረ ሐሳብ እወጃ ፎክሎርነት.‹‹በሚል ርእስ የቀረበው ጥናት መሠረት ያደረገው በ1999 ዓ.ም በአዲስ አበባ ማኀደረ ሰብሐት ቅድስት ልደታ ቤተ ክርስቲያን የነበረውን የአከባበር ሥነ ሥርዓት ነው፡፡
የባሕረ ሐሳብ ሥርዓታዊ ብያኔ፤ የዘመን መለወጫዉ ልዩ ልዩ መጠሪያዎች እንዴትነት፤ የበዓሉ ትእምርቶችና ውኩልነታቻው፤ የወራትና ቀናት ስያሜ ፎክሎሪዊ መሠረት ታትቶብታል፡፡
የባሕረ ሐሳብ እውጃው ከፎክሎር ዐበይት ተግባራት እኳያ ተመዝዘው የሚወጡ ቁምነገሮችን ጥናቱ አግኝቷል፡፡