በዳባት ገብርኤል ቤተ-መዘክር ውስጥ የሚገኙ ቁሳዊ ባህሎች መዘርዝር ከአጫጭር መግለጫ ጋር

No Thumbnail Available

Date

2001-06

Journal Title

Journal ISSN

Volume Title

Publisher

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ

Abstract

ይህ ጥናት «በዳባት ገብርኤል ቤተ-መዘክር ውስጥ የሚገኙ ቁሳዊ ባህሎች መዘርዝር ከአጫጭር መግለጫዎች ጋር» በሚል ርዕስ የቀረበ ነው፤ቤተ-መዘክሩ በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ዳባት ወረዳ እንደሚገኝና በደጅ አዝማች አያሌው ብሩ አማካኝነት እንደተመሠረተ ተቃኝቷል፤ ነገር ግን ከአቅምና ከጊዜ ውሱንነት የተነሳ የቤተ-መዘክሩን መስራችና በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ከፍተኛ ቦታ ያላቸውን የደጅ አዝማች አያሌው ብሩን የሕይወት ታሪክ ከልደት እስከ ህልፈተ ሕይወት በስፋትና በጥልቀት በዚህ የጥናት ወረቀት ማቅረብ አልተቻለም ምክንያቱም በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ካላቸው ሰፊ ቦታ አንፃር የሳቸው ታሪክ ሙሉና አዋጪ ጥናት ሊወጣው ይችላል ብሎ አጥኝው በማሰቡ ነው፡፡ ጥናቱ ቁሳዊ ባህሎቹን በአካል ቀርቦ በመመልከት፣ስለ ቤተ-መዘክሩ እውቀት ያላቸውን ሰዎች ቃለ-መጠይቅ በማድረግና አጋዥ የፎቶ ካሜራ በመጠቀም እንዲሁም በተነሱት ንድፈ ሀሣቦች ላይ በመመርኮዝ ትንታኔ በመስጠት ላይ አተኩሯል፤በውስጡስ ምን ምን ቁሳዊ ባህሎችን ይዟል፣ ቁሳዊ ባህሎቹ መቼና በማን የተበረከቱ ናቸው፣ሁሉም ቁሶች ምን ዓይነት ትዕምርታዊ ትርጓሜ አላቸው የሚሉትንና መሠል ጉዳዮች በተነሱት ንድፈ ሀሣቦች መሠረት ለመቃኘት ተሞክሯል፡፡ በቤተ-መዘክሩ ውስጥ ለእይታ ከቀረቡት ቁሳዊ ባህሎች መካከል አንዳንዶቹ ስንክናዊ ርቀታቸው /ውበታቸው ሳይደበዝዝና መግለጫ ይሆናቸው ዘንድም በወጉ የተቀናበረና የተደራጀ ታሪክ ያላቸው መሆናቸውን፤ የተወሰኑት ደግሞ ሥንክናዊ አሻራቸው ደብዝዞ ጭራሽ በማንና መቼ እንደተሠሩ፣በማን አማካኝነት እንደተበረከቱ የሚገልፅ መረጃ የሌላቸው መኖራቸውን የጥናቱ መረጃዎች አመልክተዋል፤ በመሆኑም እነዚህ ቁሳዊ ባህሎች በማህበረሰቡ ዘንድ ያላቸውን ትዕምርታዊ ትርጓሜ በመግለፅና የማጠቃለያ ሀሣብ እንዲሁም ቤተ-መዘክሩ በመልካም ጎኑ /በጥንካሬው እንዲገፋበትና ድክመቱንም ይቀርፍ ዘንድ ጥቁመታ/ የመፍትሔ

Description

Keywords

ገብርኤል ቤተ-መዘክር ውስጥ

Citation