በየካቲት 12 የመሰናዶ ትምህርት ቤት የተማሪዎች ትምህርት ነክ ያልሆኑ ጽሁፎችን የማንበብ ልምድ
dc.contributor.advisor | አስማረ, ተሻገር | |
dc.contributor.author | ገ/ኪዳን, አቤል ገ/ኪዳን | |
dc.date.accessioned | 2018-06-13T10:11:53Z | |
dc.date.accessioned | 2023-11-09T04:05:46Z | |
dc.date.available | 2018-06-13T10:11:53Z | |
dc.date.available | 2023-11-09T04:05:46Z | |
dc.date.issued | 2001-06 | |
dc.description.abstract | የዚህ ጥናት ዋና አላማ ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚገቡ ተማሪዎችን ትምህርት ነክ ያልሆኑ ጽሁፎችን የማንበብ ልምድ መመዘን ነው፡፡ ጥናቱ የተካሄደው በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ት/ቢሮ የጉለሌ ክ/ከ ት/መምሪያ ስር በሚገኘው የየካቲት 12 የመሰናዶ ት/ቤት ነው፡፡ መረጃዎችም ከመምህራን እና ከተማሪዎች በመጠይቅ አማካኝነት ተሰብስበዋል፡፡ ት/ቤቱ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ተማሪ የሚያስተናግድ ሲሆን ሁሉንም ተማሪዎች መመዘን ስለማይቻል ከ11ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል 80 ተማሪዎች በመጠይቁ ውስጥ ተካተዋል፡፡ የእነዚህን ተማሪዎች ምላሽ ለማረጋገጥም በት/ቤቱ የሚያስተምሩ 6 የቋንቋ መምህራን በመጠይቅ መረጃ እንዲሰጡ ተደርጓል፡፡ የተገኘው ውጤትም ተተንትኗል፡፡ በጥናቱ የተገኘው ውጤትም የሚያመለክተው የተማሪዎች ትምህርት ነክ ያልሆኑ ጽሁፎች የማንበብ ልምድ ዝቅተኛ እንደሆነ ነው፡፡ ለዚህም እንደ ምክንያት የሚጠቀሰው ተማሪዎች ስለ ንባብ ያላቸው ግንዛቤ እጅግ ዝቅተኛ መሆን፣ የኤሌክትሮኒክስ ሚዲያዎች ጫና፣ የትምህርት ቤቶች ንባብን በማስለመድ ረገድ ሊኖራቸው የሚገባ አስተዋጽኦ በሚገባ መወጣት አለመቻል ናቸው፡፡ ስለዚህም ወደፊት ትምህርት ነክ ያልሆኑ ጽሁፎችን የማንበብ ልምድ ለማዳበር ሊደረጉ ይገባቸዋል ብሎ አጥኚው የተወሰኑ ሀሳቦችን ሰንዝሯል፡፡ እነሱም የንባብ ክፍል ማዘጋጀት፣ ከፍተኛ ቅስቀሳ ማካሄድ እና ሳቢነት ያላቸውን ጽሁፎች በመማሪያ መጻህፍት ውስጥ ማካተት ናቸው፡፡ | en_US |
dc.identifier.uri | http://etd.aau.edu.et/handle/123456789/691 | |
dc.language.iso | am | en_US |
dc.publisher | አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ | en_US |
dc.subject | የመሰናዶ ትምህርት ቤት | en_US |
dc.title | በየካቲት 12 የመሰናዶ ትምህርት ቤት የተማሪዎች ትምህርት ነክ ያልሆኑ ጽሁፎችን የማንበብ ልምድ | en_US |
dc.type | Thesis | en_US |