የአማርኛ አፈ-ፈት ተማሪዎች አንብቦ መረዳትና መጻፍ ቅንጅታዊ ማስተማር ዘዴ የመጻፍ ችሎታን ለማሻሻል ያለው አስተዋጾ በበህር ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትበ11ኛ ክፍል ተተኳሪነት
No Thumbnail Available
Date
2023-09
Authors
Journal Title
Journal ISSN
Volume Title
Publisher
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ
Abstract
የዚህ ጥናት ዋና ዓላማ በቡታጅራ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህረት የሚማሩ የ11ኛ ክፍል ተማሪዎችን የማአንብበና የመጻፍ ችሎታ ለማዳበር የተለያዩ ልምምድ በማድረግ ያውን አስተዋጦ ለማረጋገጥ በሙከራ ማረጋገጥ ነው፡፡በጥናቱ የተካተቱ 100(መቶ) ተማሪዎች ወንድ 45 ሴት 55 የተመረጡት የአማርኛ ቋንቋ አፈ-ፈት ተማሪዎችከተለዩ በኋላ በአጣ ንሞና ዘዴተመርጠው ጠኛቱ ተከሂዶል፡፡ ለጥናቱ አስፈሊጊ መረጃዎችን ለማግኘት በተጠኚ ተማሪዎች 2 ድርሰት ፈተናዎችን እንዲጽፉ ተደርጓል፡፡ከእያንዳንዱ 50 ያህለ ታርሟል፡፡ በዚህ ድርሰት መሰረት ተማሪዎቹ የአንብቦ መረዳትና መጻፍ በቅንጅትና ማስተማር ዘዴ የተሻለ የትኛው መሆኑን ለማየት ተችሏል፡፡ በተጨማሪ በተጠኚ ተማሪዎች የጽሁፍ መጠይቅ ተሰብስቧል፡፡ በተሰበሰቡ መረጃዎች ተማሪዎች በቅንጅት ማስተማር ዘዴ የተገኘው ውጤት፡-ከማስተማሪያ ዘዴው ውጤት የተገኘው መረጃ መሰረት ጠቅላላ የውጤት ማሻሻል ያሳዩ ተማሪዎች ሲሆኑ፣ ማንበብ በቅንጅት ከተማሩ በኋላ ከ70 በላይ20 ተማሪዎች በማንበብ በተናጠል ያሻሻሉ፣ 33 በመጻፍ ማስተማር ያሻሻሉ፣ አንብቦ መረዳትና መጻፍ በቅንጅት ከተማሩ በኋላ 60 ተማሪዎች የውጤት ማሻሻል አሳይተዋል፡፡ አጠቃላይ የተገኘው ውጤት ከ70 እና ከ80 በላይ ያመጡ ተማሪዎች ናቸው፡፡ ከጽሁፍ መጠይቅ ተማሪዎች በቅድመና ድሀረ ከተማሩ በኋላ በቅንጅት መማራቸው ውጤታማ መሆኑን ያሳያል፡፡ እንዲሁም ለመፌትሔ ሀሳብ ከቀረቡት መካከል የመምህራን መማር ማስተማር ሂደት በቅንጅት ለማስተማር ትኩረት የሚሰጡ ቢሆን የተለያዩ መልመጃዎች ከመምህሩ በተጨማሪ ተማሪዎችን የሚያሳትፍ፣ የሚያነቃቃ፣ ከተማሪዎች ዳራዊ ክህሎት ጋር የተያያዘ ቢሆን፣ተማሪዎች የማንበብና የመጻፍ ክህሎታቸውን ለማዳበር በተለያዩ አጋጣሚዎች በትምህርት ልምምድ ለማድረግ ምቹ ሁኔታ ማመቻቸት የሚሉ መፍትሄ ሐሳቦች ተጠቁመዋል፡፡
Description
Keywords
የአማርኛ ቋንቋ አፈ-ፈት፣የማአንብበና የመጻፍ ችሎታ ለማዳበር