በባንጃ ወረዳወና አከባቢዋ የአዊ ቢሄረሰብ አለባበስና ጌጣጌጦች ገላጭ-ጥናት
No Thumbnail Available
Date
2004
Authors
Journal Title
Journal ISSN
Volume Title
Publisher
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ
Abstract
ይህ ጥናት በባንጃ ሀገረሰባዊ ልብስ እና ጌጣጌጦች ገላጭ ጥናት ላይ የሚያተኩር ነው
አበየት ዓላማዎቹም በአዊ ብሄረሰብ ባነጋ ወረዳና አከበአቢዋ ያሉትን አለባበስና አጋጌጥ
ውክልናችውን መመርመር በሰነድ መግለጸና እና ማሳየት ነው፡፡ንሁሳን አላማዎችን በባነጃና አከባቢዋ
ማለትም ቸውሳ ባታመርያምና ቅዳማጃ ተብለው በሚጠሩ የገጠር ቀበሌዎች ያሉ ወጣቶች እናቶችና
አባቶች ምን ምን አንደሆኑ ማሳየት ነው፡፡
እንዲሁም የጸጉር አሰራርና የውቅራትን መልክ ማሳየት የአለባበስ ስራቱን አጋጣሚዎቹን መግለጸ
የሚሉ ንዑዎችን ያካተተ ነው፡፡ከዚህ በተጭማሪም ልብሶቹን የማህበረሰቡን አባላት ማንነት እንዴት እንደሚገለጹ
ዕና በቁሶች ዙርያ እየተደረጉ ለውጦች ምን ምን እንደሆኑ ያሳያል ፡፡በዜህም የተመረጡ የጸጉር አሰራር
አስር ልብስ እና ስድስት የጌጣጌጥ ኤነቶች ተተንትነዋል፡፡
ይህ ጥናት የተነሳበትን አላማ አላማ ከግብ ለማድረስ በቃለ መጠየቅ እና በምልከታ በተሰበሰቡ ቀዳመይ መረጃዎች
የተመሰረተ ነው፡፡ጥናቱ አየንታዊ የምርምር ዘዴ እንደ መሆኑ መጠን በታላሚ ናሙና አወሳሰድ ዘዴ
ከተመረጡ እና ባህሉን ጠንቅቀው ያውቃሉ ከተባሉ ግለሰቦች ከበህል ቢሮ ሰራተኞችና የእግ ባለሞዎች በቀለ
መጠይቅ እንዲሁም ከመኖር መንደሮች እና ከገቢያ ቦታዎች በምልከታ በተወሰዱ መረጃዎች ተገነባ ነው፡፡
ከእነዚህ ቀዳማዊ ምንጮች ከተገኘ መረጃዎች በተጨማ በጥናቱ ጉዳይ የተያዙ የጥናት ውጤቶች
እንዲሁም ከመጠሀፍት የተገኝ ሐሳቦችንም ካትታል፡፡
የአከባቢው ሐገረሰባዊ ልብእሶች ከቁሳው ፋዳዎችው በተጨማሪ በባህሉ ባለቤቶች ዘንድ
የሚታወቁ ተምሳሌታዊ ፋይዳዎች ያላችው ከመሆናቸውም በላይ የተለዩ የማህበራዊና
ኢኮኖሚያዊ ደረጋዎችን የሚያመለክት ትምህርቶች ሆነውየገለግላሉ ፡፡በሚያስተላልፉት መልክት
አማከይነትም እድሜን የማሳወቅ ማህበራዊን ደረጃዎችን ለማሳየት ከእርኩስ መንፈስ የመከላከል እናትነትን
እና የተለያዩ ማህበራዊ ሁኔታዎችን የማሳወቅ ፋይዳ ያላችው መሆኑ በጥናቱ ተገጻል፡፡