<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?>
<rdf:RDF xmlns:rdf="http://www.w3.org/1999/02/22-rdf-syntax-ns#" xmlns="http://purl.org/rss/1.0/" xmlns:sy="http://purl.org/rss/1.0/modules/syndication/" xmlns:dc="http://purl.org/dc/elements/1.1/" xmlns:taxo="http://purl.org/rss/1.0/modules/taxonomy/">
  <channel>
    <title>DSpace Collection: Thesis - Ethiopian Literature &amp; Folklore</title>
    <link>http://etd.aau.edu.et:80/dspace/handle/123456789/410</link>
    <description />
    <items>
      <rdf:Seq>
        <rdf:li resource="http://etd.aau.edu.et:80/dspace/handle/123456789/4357" />
        <rdf:li resource="http://etd.aau.edu.et:80/dspace/handle/123456789/4355" />
        <rdf:li resource="http://etd.aau.edu.et:80/dspace/handle/123456789/4354" />
        <rdf:li resource="http://etd.aau.edu.et:80/dspace/handle/123456789/4353" />
      </rdf:Seq>
    </items>
  </channel>
  <textInput>
    <title>The Collection's search engine</title>
    <description>Search the Channel</description>
    <name>search</name>
    <link>http://etd.aau.edu.et:80/dspace/simple-search</link>
  </textInput>
  <item rdf:about="http://etd.aau.edu.et:80/dspace/handle/123456789/4357">
    <title>በደጋ ዳሞት ወረዳ የእረኞች ግጥም ይዘት ትንተና</title>
    <link>http://etd.aau.edu.et:80/dspace/handle/123456789/4357</link>
    <description>Title: በደጋ ዳሞት ወረዳ የእረኞች ግጥም ይዘት ትንተና
&lt;br/&gt;
&lt;br/&gt;Authors: ሙሉቀን, ጌትነት
&lt;br/&gt;
&lt;br/&gt;Abstract: ደጋዳሞት በምዕራብ ጐጃም ውስጥ ከሚገኙ ወረዳዎች አንዱ ነው፡፡ ወረዳው&#xD;
ከአዲስ አበባ 391 ኪ.ሜ በምዕራብ፣ ከባህር ዳር ደግሞ 266 ኪ.ሜ በምስራቅ በኩል&#xD;
ይገኛል፡፡ ወረዳው በስተሰሜን ከቢቡኝ ወረዳ፣ በስተደቡብ የጃቢጠህናንና የደምበጫ&#xD;
ወረዳዎች፣ በምስራቅ የደምበጫ ወረዳ፣ በምዕራብ የቋሪትና የቢቡኝ ወረዳ ያዋስነዋል፡፡&#xD;
ከወረዳው ማስታወቂያ ጽ/ቤት ያገኘሁት መረጃ እንደሚያመለክተው በወረዳው&#xD;
ውስጥ የሰፈረው ህዝብ ቁጥር 197,007 ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ በወረዳው ውስጥ ያለው&#xD;
የነዋሪ ቁጥር እየጨመረ መሄዱን ያገኘሁት መረጃ ያሳያል፡፡ በወረዳው ውስጥ 32&#xD;
ቀበሌዎች አሉ፡፡ ከእነዚህም 32 ቀበሌዎች መካከል አንድ የከተማ ቀበሌ አለ፡፡ በዚህ&#xD;
የከተማ ቀበሌ ውስጥ የሚኖረው የህዝብ ቁጥር 3,474 የሚሆንነው፡፡ በወረዳው ውስጥ&#xD;
ያሉ 31 የገጠር ቀበሌዎች የህዝብ ቁጥር ብዛት ደግሞ 193,533 የሚሆን ህዝብ እንዳለ&#xD;
ከወረዳው ማስታወቂያ ጽ/ቤት የተገኘው መረጃ ያሳያል፡፡&#xD;
ደጋዳሞት ደጋ ነው፡፡ ደጋዳሞት የሚለውን ስያሜ ያገኘውም ደጋ ከመሆኑ የተነሳ&#xD;
ነው፡፡ ወረዳው በአንዳንድ ወቅት ከተለመደው በላይ ቅዝቃዜ ይታይበታል፡፡ በህዳር እና&#xD;
በታህሳስ ያለው ቅዝቃቄ ከሌላው ጊዜ የተለየ ነው፡፡ በእነዚህ ወቅቶች የአካባቢው መሬት&#xD;
በሙሉ በውርጭ ይሸፈናል፡፡ የአካባቢው ነዋሪ ቅዝቃዜውን የለመደው ቢሆንም እንዳንድ&#xD;
ጊዜ ከበረታ ሙቀትያላቸውን ልብሶች ይለብሳል፡፡ ከየልብሱ ቁርጥራጭ በሚያያዝና&#xD;
በመስፋት ድሪቶ፣ ካፖርት፣ጎጃምአዘነ ወዘተ ይለብሳሉ፡፡&#xD;
በወረዳው የተለመደው የቤት አሰራር ቆርቆሮ ቤት እና ጎጆ ቤት ነው፡፡ ጎጆቤት&#xD;
ግድግዳው ከእንጨትና ከጭቃ ጣሪው ከገብስ ብርዕ የሚሰራ ሲሆን ቆርቆሮ ቤት&#xD;
ግድግዳው ከእንጨትና ከጭቃ፣ ጣሪያው ላይ ቆርቆሮ በመምታት ይሰራል፡፡ ቆርቆሮ ቤት&#xD;
ሲያረጅ እንዳይወድቅ በማሰብ በግርግዳው ዙሪያ ድንጋይ ይከቡበታል፡፡ ቆርቆሮቤት&#xD;
በአካባቢው ዋና መኖሪያ አድርገው ይጠቀሙታል፡፡ ቆርቆሮ ቤት ያለው ሰው ሁሉ&#xD;
ጎጆቤት አለው፡፡ ጎጆ ቤት በአሁኑ ጊዜ እንደ ማብሰያ ቤት የሚጠቀሙት ቢኖሩም ዋና&#xD;
መኖሪያ ቤት ያደረጉት ብዙዎች አሉ፡፡</description>
  </item>
  <item rdf:about="http://etd.aau.edu.et:80/dspace/handle/123456789/4355">
    <title>የመመረቂያ መፅሔት ፎቶግራፎች ግርጌ ፅሑፎች፣ የይዘት ትንተና (ከ1996 - 2001)</title>
    <link>http://etd.aau.edu.et:80/dspace/handle/123456789/4355</link>
    <description>Title: የመመረቂያ መፅሔት ፎቶግራፎች ግርጌ ፅሑፎች፣ የይዘት ትንተና (ከ1996 - 2001)
&lt;br/&gt;
&lt;br/&gt;Authors: ረድኤት, እሸቴ
&lt;br/&gt;
&lt;br/&gt;Abstract: በአጋጣሚም ሆነ ባለኝ የማህበራዊ ግንኙነት ሳቢያ በተለያዩ ጊዜያት ከተመራቂ ተማሪዎች&#xD;
ጋር የደስታቸው ተካፋይ በመሆን ብዙ ጊዜያትን አሳልፌያለሁ፡፡ አብዛኛውን ጊዜ&#xD;
የመመረቂያ መጽሔቶቻቸውን በግሌ፣ ከተመራቂዎቹ እንዲሁም በዝግጅቱ ላይ ከተገኙ&#xD;
ሰዎች ጋር በመሆን መጽሔቶቹን የመመልከት እና በፎቶግራፎቹ ስር የተፃፉትን ጽሁፎች&#xD;
(captions) የማንበብ ልምድ ነበረኝ፡፡ መጽሔቶቹን በማገላብጥበት ወቅት በይበልጥ&#xD;
ትኩረቴን የሚስቡት በፎቶግራፎቹ ግርጌ የሰፈሩት ፅሁፎች አንዳች ስሜትንም በውስጤ&#xD;
ያጭሩብኝ ነበር፡፡ በተለይ የስነ-ፅሁፍ ተማሪ ከሆንኩኝ በኋላ ዕሁፎቹን ከምማረው&#xD;
ትምህርት ጋር በማዛመድ ማጤን ጀመርኩ፡፡ ይህም በእነዚህ ፅሁፎች ላይ ጥናት&#xD;
እንዳደርግ አነሳስቶኛል፡፡&#xD;
በተጨማሪም ለዚህ ጥናት ያነሳሳኝ የመመረቂያ መጽሔቶች የፎቶግራፍ ግርጌ ፅሁፎች&#xD;
እንደ መቃብር ላይ ጽሁፎች፣ የግድግዳ ላይ ጽሁፎች ወ.ዘ.ተ በስፋት ተሰብስበው በጥናት&#xD;
ተደግፈው በሚፈለገው መጠን አለመገኘታቸው ነው፡፡</description>
  </item>
  <item rdf:about="http://etd.aau.edu.et:80/dspace/handle/123456789/4354">
    <title>ብድሯን ያልከፈለች ወፍ እና ሆዳሙ ጅብና ሌሎች የአያ ጅቦ ታሪኮች ላይ የቀረበ የጭብጥ ትንተና</title>
    <link>http://etd.aau.edu.et:80/dspace/handle/123456789/4354</link>
    <description>Title: ብድሯን ያልከፈለች ወፍ እና ሆዳሙ ጅብና ሌሎች የአያ ጅቦ ታሪኮች ላይ የቀረበ የጭብጥ ትንተና
&lt;br/&gt;
&lt;br/&gt;Authors: ዓለም, ከበደ
&lt;br/&gt;
&lt;br/&gt;Abstract: አንድ ጽሁፍ ሲፃፍ የአንባቢው ወይም የተደራሲው ማንነትና የአስተሳሰብ ደረጃ&#xD;
በሚገባ ሊጤን ይገባዋል፡፡ ይህም ሲባል ደራሲ የሚጽፈውን ጽሁፍ ሁሉ በራሱ&#xD;
ገጠመኝና የእውቀት ደረጃ ብቻ የሚጽፍ ከሆነ የጽሁፉ የመነበብ እድል ያነሰ ይሆናል፡፡&#xD;
ለህፃናት የሚፃፉ ጽሁፎች አብዛኛውን ጊዜ የሚፃፉት በአዋቂ ሰዎች ሲሆኑ&#xD;
በውስጣቸውም ማኀበረሰቡ ለልጆቹ ማስተላለፍ ስለሚፈልገው ጉዳይ ወይም በሕይወቱ&#xD;
ውስጥ ትልቅ ቦታ ለሚሰጡት እሴቶቹ ቀጣይነት እንዲኖረው በመፈለግ ለልጆቹ&#xD;
(ለሕፃናት) ተመራጭ በሆነው ዘውግ በተረት መልክ በመቅረጽ ስለባህሉ፤ ሥነ ምግባሩ፤&#xD;
ወዘተ ለልጆቹ ያቀርባል፡፡ ይህም ልጆች በብዛት በተረቶች ስለሚሳቡና ስለሚዝናኑ&#xD;
ማስተማር የፈለገውን ነገር በቀላሉ ለልጆት ትምህርት በማይመስል መልኩ ለማቅረብና&#xD;
ለማስረጽ ስለሚረዳው ነው፡፡ ይህም የተሳካ ይሆን ዘንድ የህፃናቱ የአእምሮ ብስለት&#xD;
ደረጃ ያገናዘቡ እና ጉዳዩን የማቅረቢያ (የመባያ) መንገዱም ቢሆን ህፃናቶቹ በደንብ&#xD;
በሚያውቃቸው በሚወዷቸው በጨዋታቸውም ወቅት በሚጠሯቸው ነገሮች መሆን&#xD;
ይኖርባቸዋል፡፡&#xD;
በሀገራችንም በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ ደራሲያን ለህፃናት ተብለው የተፃፉ&#xD;
በርካታ መፃህፍት አሉ፡፡ በዚህ ጥናት ውስጥ የምናየው ግን በ2ዐዐ0 ዓ.ም በዓለም እሸቱ&#xD;
የተፃፈውን ሆዳው ጅብና ሌሎች የአያ ጅቦ ታሪኮች እና በ2ዐዐ1 ዓ.ም በውድአላት&#xD;
ገዳሙ የተፃፈውን ብድሯን ያልከፈለች ወፍ በተሰኙት የተረት መፃህፍት ይሆናል፡፡</description>
  </item>
  <item rdf:about="http://etd.aau.edu.et:80/dspace/handle/123456789/4353">
    <title>የውስጥ አርበኞች ገፀባህሪያት አቀራረብ በተመረጡ የአማርኛ ልቦለዶች</title>
    <link>http://etd.aau.edu.et:80/dspace/handle/123456789/4353</link>
    <description>Title: የውስጥ አርበኞች ገፀባህሪያት አቀራረብ በተመረጡ የአማርኛ ልቦለዶች
&lt;br/&gt;
&lt;br/&gt;Authors: ዘቢባ, ነስሩ
&lt;br/&gt;
&lt;br/&gt;Abstract: ይህ ጥናታዊ ፅሁፍ በረመጥና በጣምራ ጦር እና በየልምዣት ልቦለዶች ላይ&#xD;
የተሠራ ሲሆን ትኩረት የሚያደርገው በልቦለዱ ውስጥ ባሉ የውስጥ አርበኞች&#xD;
ገፀባህሪያት አቀራረብ ላይ ነው፡፡&#xD;
ጥናታዊ ጽሁፍ አራት ምዕራፎች አሉት ምዕራፍ አንድ ላይ የጥናቱ ዳራ፣&#xD;
የጥናቱ አላማ፣የጥናቱ ዘዴ፣ የጥናቱ ወሰን፣ የጥናቱ አስፈላጊነት እና የጥናቱ አነሳሽ&#xD;
ምክንያት ተካተዋል፡፡ ሁለተኛው ክፍል ደግሞ ክለሳ ድርሳናት ማለትም የተዛማጅ&#xD;
ጥናቶች ቅኝት ንድፈ ሀሳባዊ ዳራ አለ፡፡&#xD;
በምዕራፍ ሦስት ለጥናቱ በተመረጡት ሦስት ልቦለዶች ትንተና ይሰጥባቸዋል፡፡&#xD;
ትንተናው የሚከናወነው የገፀባህሪያቱን አቀራረብ በማጤን ይሆናል፡፡&#xD;
ጥናቱ ለትንተናው በቀረቡት መጸሐፍት (በረመጥ፣በጣምራ ጦር እና በየልምዣት)&#xD;
ውስጥ የምናገኛቸውን የውስጥ አርበኞች ገፀባህሪያት አቀራረብ ይተነትናል፡፡&#xD;
1.1 የጥናቱ ዳራ&#xD;
ለጥናቱ የተመረጡት ልቦለዶች ረመጥ እና ጣምራ ጦር በጦርነት ታሪክ ላይ&#xD;
ተመሰርተው የተፃፉ ሲሆን የልምዣት ደግሞ የተመረጠበት ምክንያት በልቦለድ ታሪክ&#xD;
ላይ የውስጥ አርበኛ ገፀባህሪ ስለሚገኝ ነው፡፡&#xD;
ረመጥ ታሪካዊ ልቦለድ ሲሆን ፈጠራ ታክሎበት ታሪካዊ ልቦለድ ሆኗል፡፡&#xD;
መጽሐፉ የተፃፈ በቀኝ አዝማች ታደሰ ዘወልዴ እና በገበየሁ አየለ ነው፡፡ የመጽሐፉ&#xD;
ታሪክ የሚያተኩረው በ1928ቱ የፋሽሲት ኢጣሊያ ወረራ ወቅት ላይ ነው፡፡&#xD;
ጣምራ ጦር በገበየሁ አየለ የተፃፈ መጽሐፍ ነው፡፡ ታሪኩ 1969-70 የነበረውን&#xD;
የኢትዮጵያንና የሶማሊያን ጦርነት መሠረት አድርጐ የተፃፈ ልቦለድ ነው፡፡&#xD;
የልምዣት በ1980 የታተመ በሀዲስ አለማየሁ የተፃፈ ልቦለድ ነው፡፡</description>
  </item>
</rdf:RDF>

